From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ከጥንት ፡ እንደሰማሁት
በዓይኖቼም ፡ ደግሞ ፡ እንዳየሁት
አምላክ ፡ ከአንተ ፡ በቀር ፡ የለም
መቼም ፡ ቢሆን ፡ አይገኝም
በምድር ፡ ሆነ ፡ በሠማይ
በየብስ ፡ ሆነ ፡ በባሕር ፡ ላይ
በሰው ፡ ልጆችም ፡ መካከል
የለም ፡ አንተን ፡ የሚስተካከል
አዝ፦ ከፍ ፡ በል ፡ ለዘለዓለም ፡ ከፍ ፡ በል (፬x)
አምላኬ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ንጉሤ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ጌታዬ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ የማመልከው ፡ የለም
ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ የማመልከው ፡ የለም (፪x)
ሰዎች ፡ የሚያመልኳቸው
ዛሬም ፡ የሚከተሏቸው
ብዙ ፡ አማልክት ፡ ቢሆኖሩም
አንዳቸውም ፡ እውነት ፡ አይደሉም
ታላቅ ፡ ገናና ፡ ኃይለኛ ፡ (ገናና ፡ ኃይለኛ)
ታጋሽ ፡ መሃሪ ፡ ሞሆንህ
ከጥንት ፡ ከጥንትም ፡ ጀምሮ ፡ (ጀምሮ)
በእውነት ፡ እግዚአብሔር ፡ አምላክ ፡ ነህ
አዝ፦ ከፍ ፡ በል ፡ ለዘለዓለም ፡ ከፍ ፡ በል (፬x)
አምላኬ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ንጉሤ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ጌታዬ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለዘለዓለም
ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ የማመልከው ፡ የለም
ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ የማመልከው ፡ የለም (፪x)
በእኔ ፡ ላይ ፡ ተሹመሃል
ፍቅርህ ፡ ልቤን ፡ ወርሶታል
እውነት ፡ በርታልኛለች
ነፍሴም ፡ አምላኳን ፡ አውቃለች
ውዴ ፡ አንተ ፡ የእኔ ፡ ነህ
እኔም ፡ የአንተ ፡ ሆኛለሁ
በቀረልኝ ፡ ዘመን ፡ ሁሉ
ሳደንቅህ ፡ ሳከብርህ ፡ ኖራለሁ
አዝ፦ ከፍ ፡ በል ፡ ለዘለዓለም ፡ ከፍ ፡ በል (፰x)
ጌታ ፡ ሆይ ፡ እናከብርሃለን ፣ ከፍ ፡ እናረግሃለን ።
አንተ ፡ ብቻ ፡ ታላቅ ፡ ነህና ፤
አንተ ፡ ብቻ ፡ ጌታ ፡ ነህና ፤
አንተ ፡ ብቻ ፡ አምላክ ፡ ነህና ።
ኦ ፡ ከፍ ፡ አናደርግሃለን ፣ ክበር ፡ እንልሃለን ፣
ስለ ፡ አምላክነትህ ፡ እንሰግዳለን ፤
ስለ ፡ ጌትነት ፡ እንሰግዳለን ፤
ምህረትህን ፡ አይተናልና ኢየሱስ ።
ኦ ፡ ፍቅርህን ፡ ቀምሰናልና ፡ በሕይወታችን
ልንክደው ፡ የማንችለው ፡ እውነት ፡ በርቶልናልና ፡ ኢየሱስ ፤
ከፍ ፡ ካለው ፡ በላይ ፡ ከፍ ፡ እናደርግሃለን
ኦ ፡ ሃሌሉያ !
|