ስሙን ፡ አከብራለሁ (Semun Akebralehu) - እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ
(Endalkachew Hawaz)

Endalkachew Hawaz 3.jpg


(3)

እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው
(Egziabhier Teleq New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ ፡ አልበሞች
(Albums by Endalkachew Hawaz)

 
በሃዘን ፡ ፈንታ ፡ ደስታ
በለቅሶም ፡ ምትክ ፡ ዕልልታ
ሁሉንም ፡ መልካም ፡ አደረገው
ክፉውን ፡ ለበጐ ፡ ቀየረው (፪x)

አዝ፦ ምን ፡ ልበል ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ
ምሥጋናዬን/አምልኮዬን ፡ ለጌታ ፡ ላሰማ (፪x)
በምሥጋና ፡ ስሙን ፡ አከብራለሁ (፪x)
እጅግ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው
ለእኔ ፡ ያደረገው ፣ ለእኔ ፡ ያደረገው
እጅግ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው
ለእኔ ፡ ያደረገው ፣ ለእኔ ፡ ያደረገው

የተዘጋውን ፡ ደጅ ፡ ከፈተው
የነሃሱንም ፡ መዝጊያ ፡ ሰበረው
መወርወሪያዎቹን ፡ ቆራርጦ
አሳለፈኝ ፡ ከፊቴ ፡ ወጥቶ

አዝ፦ ምን ፡ ልበል ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ
ምሥጋናዬን/አምልኮዬን ፡ ለጌታ ፡ ላሰማ (፪x)
በምሥጋና ፡ ስሙን ፡ አከብራለሁ (፪x)
እጅግ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው
ለእኔ ፡ ያደረገው ፣ ለእኔ ፡ ያደረገው
እጅግ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው
ለእኔ ፡ ያደረገው ፣ ለእኔ ፡ ያደረገው

በከበረው ፡ ደሙ ፡ ቀድሶ
መንፈሱን ፡ በላዬ ፡ አፍሶ
ሕይወቴን ፡ በፍቅሩ ፡ ቀየረው
ታሪኬን ፡ እንዲህ ፡ አሳመረው (፪x)

አዝ፦ ምን ፡ ልበል ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ
ምሥጋናዬን/አምልኮዬን ፡ ለጌታ ፡ ላሰማ (፪x)
በምሥጋና ፡ ስሙን ፡ አከብራለሁ
በምሥጋና ፡ ስሙን ፡ አከብራለሁ
እጅግ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው
ለእኔ ፡ ያደረገው ፣ ለእኔ ፡ ያደረገው (፬x)