በእግዚአብሔር ፡ የተወደደ (Begziabhier Yetewedede) - እንዳልካቸው ፡ ሐዋዝ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳልካቸው ፡ ሐዋዝ
(Endalkachew Hawaz)

Endalkachew Hawaz 3.jpg


(3)

እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው
(Egziabhier Teleq New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳልካቸው ፡ ሐዋዝ ፡ አልበሞች
(Albums by Endalkachew Hawaz)

 
አዝ፦ በእግዚአብሔር ፡ የተወደደ ፡ በእርሱ ፡ ዘንድ ፡ ይኖራል (፪x)
ከትከሻው ፡ መሃል ፡ ተማምኖ ፡ ያድራል (፪x)

ለሚታመኑበት ፡ መታመኛ (ኦሆ ፡ መታመኛ)
ነውና ፡ የሚያኮራ ፡ መልካም ፡ እረኛ (ኦሆ ፡ መልካም ፡ እረኛ)
እኔም ፡ ከጥላው ፡ በታች ፡ ተጠልያለሁ (ኦሆ ፡ ተጠልያለሁ)
ፅኑ ፡ ክንዱን ፡ ተደግፌ ፡ አመልከዋለሁ (ኦሆ ፡ አመልከዋለሁ)

አምላኬ ፡ መታመኛዬ ፡ በእርሱ ፡ እደገፋለሁ
የፀና ፡ ግንብ ፡ ነውና ፡ በሥሙ ፡ እጓደዳለሁ
ገና ፡ ነፍሴ ፡ ትጠግባለች ፡ ከማያልቀው ፡ ቸርነቱ
በዘይት ፡ ሊያለመልመኝ ፡ ተክሎኛል ፡ እና ፡ በቤቱ

እርሱን ፡ ተማምኜው ፡ እኖራለሁ
በክንፉቹ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አርፌያለሁ (፪x)

አዝ፦ በእግዚአብሔር ፡ የተወደደ ፡ በእርሱ ፡ ዘንድ ፡ ይኖራል (፪x)
ከትከሻው ፡ መሃል ፡ ተማምኖ ፡ ያድራል (፪x)

ለሚታመኑበት ፡ መታመኛ (ኦሆ ፡ መታመኛ)
ነውና ፡ የሚያኮራ ፡ መልካም ፡ እረኛ (ኦሆ ፡ መልካም ፡ እረኛ)
እኔም ፡ ከጥላው ፡ በታች ፡ ተጠልያለሁ (ኦሆ ፡ ተጠልያለሁ)
ፅኑ ፡ ክንዱን ፡ ተደግፌ ፡ አመልከዋለሁ (ኦሆ ፡ አመልከዋለሁ)

የሕይወትን ፡ ምንጭ ፡ አግኝቼ ፡ ከተድላው ፡ ፈሳሽ ፡ ጠጥቼ
ዳግመኛ ፡ እኔ ፡ አልጠማም ፡ ረቻለሁ ፡ ለዘለዓለም
በብርሃኑ ፡ ብርሃን ፡ አየሁ ፡ ጨለማውም ፡ ተሸነፈ
ተማምኜ ፡ እኖራለሁ ፡ ልቤ ፡ በእርሱ ፡ ስላረፈ

እርሱን ፡ ተማምኜው ፡ እኖራለሁ
በክንፉቹ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አርፌያለሁ (፬x)

ለሚታመኑበት ፡ መታመኛ (ኦሆ ፡ መታመኛ)
ነውና ፡ የሚያኮራ ፡ መልካም ፡ እረኛ (ኦሆ ፡ መልካም ፡ እረኛ)
እኔም ፡ ከጥላው ፡ በታች ፡ ተጠልያለሁ (ኦሆ ፡ ተጠልያለሁ)
ፅኑ ፡ ክንዱን ፡ ተደግፌ ፡ አመልከዋለሁ (ኦሆ ፡ አመልከዋለሁ)

እርሱን ፡ ተማምኜው ፡ እኖራለሁ
በክንፉቹ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አርፌያለሁ (፬x)