አመልክሃለሁ ፡ የእኔ ፡ ጌታ (Amelkehalehu Yenie Gieta) - እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ
(Endalkachew Hawaz)

Endalkachew Hawaz 3.jpg


(3)

እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው
(Egziabhier Teleq New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ ፡ አልበሞች
(Albums by Endalkachew Hawaz)

 
በሰማይ ፡ አየሁ ፡ አንተን ፡ የሚመስልህ ፡ የለም
በምድርም ፡ አየሁ ፡ አንተን ፡ የሚመስልህ ፡ የለም
ከምድር ፡ በታችም ፡ አየሁ ፡ አንተን ፡ የሚመስልህ ፡ የለም

በልጠህብኛልና ፡ መርጬሃለሁ
ተሽለኸኛልና ፡ ተከትዬሃለሁ
በዘመኔ ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ እገዛለሁ
ለአንተ ፡ እገዛለሁ (፬x)

አዝ፦ አመልክሃለሁ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
አመልክሃለሁ ፡ የእኔ ፡ ወዳጅ
እንደአንተ ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም
ለእኔ ፡ የሚበጅ
(፪x)
አንተን ፡ ብቻ ፡ ጌታ ፡ አመልካለሁ
ለአንተ ፡ ብቻ ፡ ኢየሱስ ፡ እገዛለሁ
ከአንተ ፡ ውጬ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ አምላክ ፡ የለኝም (፬x)

ከማን ፡ ጋር ፡ አንተን ፡ ጌታ ፡ አስተካክላለሁ
ከምን ፡ ጋር ፡ አንተን ፡ ኢየሱስ ፡ አመሳስላለሁ
ከየትኛውስ ፡ ጋራ ፡ አንተን ፡ አወዳድራለሁ

ከብርና ፡ ከወርቅ ፡ ፍቅርህ ፡ በልጦብኛል
ከሃጣን ፡ ድንኳን ፡ ይልቅ ፡ ቤትህ ፡ ተሽሎኛል
ወደአንተ ፡ መጠጋቴ ፡ ለእኔስ ፡ በጅቶኛል (፬x)

አዝ፦ አመልክሃለሁ (የእኔ ፡ ጌታ) ፡ የእኔ ፡ ጌታ
አመልክሃለሁ (የእኔ ፡ ወዳጅ) ፡ የእኔ ፡ ወዳጅ (የእኔ ፡ ወዳጅ)
እንደአንተ ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም
ለእኔ ፡ የሚበጅ
(፬x)
አንተን ፡ ብቻ ፡ ጌታ ፡ አመልካለሁ
ለአንተ ፡ ብቻ ፡ ኢየሱስ ፡ እገዛለሁ
ከአንተ ፡ ውጬ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ አምላክ ፡ የለኝም (፰x)