አገልጋይ (Agelgay) - ኤልያስ ፡ ገመቹ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤልያስ ፡ ገመቹ
(Elias Gemechu)

Elias Gemechu 1.jpg


(1)

ሳይጨልም
(Saychelem)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2013)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 6:00
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤልያስ ፡ ገመቹ ፡ አልበሞች
(Albums by Elias Gemechu)

የአምላክን ፡ ስጸሜ ፡ መልካሙን ፡ አላሚ
በትጋት ፡ አገልጋይ ፡ ብድራቱን ፡ የሚያይ
አገልጋይ
መቼ ፡ ቆረቆረው ፡ የምድር ፡ ላይ ፡ ትግሉ
አምላኩን ፡ የሚወድ ፡ የሚኖር ፡ በቃሉ
አገልጋይ

ድንገት ፡ ተፈትኖ ፡ ቢቀርብ ፡ በሚዛኑ
የሚገፋው ፡ በዛ ፡ ጠፋ ፡ ገላጋዩ
እግዚአብሔር ፡ ጠፋው ፡ ብለው ፡ ተናገሩ
በብርታቱ ፡ ጊዜ ፡ አለህ ፡ ወይ ፡ ያላሉ (፪x)

እኔ ፡ ነኛ ፡ ሰው ፡ ማረኝ ፡ በመስቀል ፡ የሞትክልኝ
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (፪x)

በቅንነት ፡ ያገለገልኩህ
ሥምህን ፡ በመጥራት ፡ የተከተልኩህ
ሊደክም ፡ ነው ፡ ዛሬ ፡ ጉልበቴ ፡ ጉልበቴ
አስበኝ ፡ አስበኝ ፡ ኢየሱስ ፡ አባቴ (፪x)

እኔ ፡ ነኛ ፡ ሰው ፡ ማረኝ ፡ በመስቀል ፡ የሞትክልኝ
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (፪x)

የአምላክን ፡ ስጸሜ ፡ መልካሙን ፡ አላሚ
በትጋት ፡ አገልጋይ ፡ ብድራቱን ፡ የሚያይ
አገልጋይ
መቼ ፡ ቆረቆረው ፡ የምድር ፡ ላይ ፡ ትግሉ
አምላኩን ፡ የሚወድ ፡ የሚኖር ፡ በቃሉ
አገልጋይ

ድንገት ፡ ተፈትኖ ፡ ቢቀርብ ፡ በሚዛኑ
የሚገፋው ፡ በዛ ፡ ጠፋ ፡ ገላጋዩ
እግዚአብሔር ፡ ጠፋው ፡ ብለው ፡ ተናገሩ
በብርታቱ ፡ ጊዜ ፡ አለህ ፡ ወይ ፡ ያላሉ (፪x)

እኔ ፡ ነኛ ፡ ሰው ፡ ማረኝ ፡ (ማረኝ)
በመስቀል ፡ የሞትክልኝ ፡ (የሞትክልኝ)
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (አትርሳው ፡ የትላንቱን)
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (፪x)

አትርሳው ፡ የትላንቱን (፫x)

አንተ ፡ በሰራኸው ፡ እራሱን ፡ ሲያሳይ
የአንተን ፡ መንገድ ፡ ትቶ ፡ በራሱ ፡ ሲዋኝ
ስለራሱ ፡ ሲያውጅ ፡ ጉራውን ፡ ሲነዛ
ስንቱ ፡ መና ፡ ቀረ ፡ ስንቱ ፡ ሆነ ፡ ጤዛ (፪x)

እኔ ፡ ነኛ ፡ ሰው ፡ ማረኝ ፡ (ማረኝ)
በመስቀል ፡ የሞትክልኝ ፡ (የሞትክልኝ)
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (አትርሳው ፡ የትላንቱን)
በፍቅር ፡ የፈለኩህን ፡ አትርሳው ፡ የትላንቱን (፪x)

አትርሳው ፡ የትላንቱን (፫x)