ምንኛ ፡ ብትወደኝ (Menegna Bitwedegn) - ኤልያስ ፡ አብጤ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤልያስ ፡ አብጤ
(Elias Abte)

Lyrics.jpg


(1)

የሚጤስ ፡ ጧፌን ፡ አላጠፋም
(Yemitesewen Tuafen Alatefam)

ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤልያስ ፡ አብጤ ፡ አልበሞች
(Albums by Elias Abte)

ከእኔ ከእሾሃማው ግራር እንጨት
ለቃልህ ማደሪያ ታቦት መስራት
ምንኛ ብትወደኝ ይህን አሰብክ
ታላቅ ውለታህን በእኔ ፈጸምክ
ስትቀርፀኝ ጣትህን አየች አይኔ
ተመስገን መድህኔ

እሾሄ ተራግፎ መቀመጫህ ሲለሰልስ
በልቤ ዙፋን ተቀምጠህ ስትነግስ
የእሾሁ ገበሬ ፊቱ ጠቁሮ ተናደደ
የድካሙ ዋጋ ሳያገኘው ሲዖል ሄደ

ከእኔ ከእሾሃማው ግራር እንጨት
ለቃልህ ማደሪያ ታቦት መስራት
ምንኛ ብትወደኝ ይህን አሰብክ
ታላቅ ውለታህን በእኔ ፈጸምክ
ስትቀርፀኝ ጣትህን አየች አይኔ
ተመስገን መድህኔ

በጨለመው ልቤ ተንሰራፍተህ ስትቀመጥ
አሮጌ ኑሮዬን በአንድ ጊዜ ስትለዋውጥ
እግሬም ተራመደ በህይወቴ ብርሃን በራ
ቀድሞ ያጨለመኝ ያ ጠላቴ ሊያየኝ ፈራ

ከእኔ ከእሾሃማው ግራር እንጨት
ለቃልህ ማደሪያ ታቦት መስራት
ምንኛ ብትወደኝ ይህን አሰብክ
ታላቅ ውለታህን በእኔ ፈጸምክ
ስትቀርፀኝ ጣትህን አየች አይኔ
ተመስገን መድህኔ

ለማይታሰብ ፍጡር የእርግማን ዛፍ የነበርኩኝ
ዛሬ በምህረት ህ ለማደሪያህ ተመረጥኩኝ
እንዲህ ከወደድከኝ እሾሄንም ካራገፍከው
የምለው የለኝም ክቡር ስምህን አከብራለሁ


ከእኔ ከእሾሃማው ግራር እንጨት
ለቃልህ ማደሪያ ታቦት መስራት
ምንኛ ብትወደኝ ይህን አሰብክ
ታላቅ ውለታህን በእኔ ፈጸምክ
ስትቀርፀኝ ጣትህን አየች አይኔ
ተመስገን መድህኔ

የከነረው መዝገብ በሸክላው ውስጥ አስቀመጥከው
ተናዳፊውን ሰዉ የክብር ቤት አደረከው
አይኖችህ ከአርያም ወደ ምድር ሲጎበኙ
ተመስገን ኢየሱሴ እኔን ከጉድጓድ አገኙ

ከእኔ ከእሾሃማው ግራር እንጨት
ለቃልህ ማደሪያ ታቦት መስራት
ምንኛ ብትወደኝ ይህን አሰብክ
ታላቅ ውለታህን በእኔ ፈጸምክ
ስትቀርፀኝ ጣትህን አየች አይኔ
ተመስገን መድህኔ