አብርሃም ፡ ቢያረጅ ፡ አታረጅም (Abraham Biyarej Atarejem) - ኤልያስ ፡ አብጤ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤልያስ ፡ አብጤ
(Elias Abte)

Lyrics.jpg


(1)

የሚጤስ ፡ ጧፌን ፡ አላጠፋም
(Yemitesewen Tuafien Alatefam)

ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤልያስ ፡ አብጤ ፡ አልበሞች
(Albums by Elias Abte)

ሽምግልናዬን ጌታዬ ሆይ አድስ
የሕይወቴን ጎዳና ወደ ተስፋህ መልስ
በእምነቴም በኑሮ እንዲሁ አርጅቻለሁ
ዛሬ በአንተ መታደስን እሻለሁ
ለአብርሃም አከብርሃለሁ
ዘርህን አበዛለሁ
ብለህ በተስፋ ስትጠራው
ዘሩን ልታበዛው
ተስፋው ሲዘገይ ከሳራ ጋር አብሮ ተማከረ
እርጅናው ሲዘምር ከተስፋው ቃል ጥቂት ፈቀቅ አለ

አብርሃም ቢያረጅ አታረጅም
ሽምግልና አንተን አያውቅ ህም
እንደተናገርክ ታደርጋለህ
ሸለቆዬን በውሃ ትሞላለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትኖራለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትሰራለህ

ሽምግልናዬን ጌታዬ ሆይ አድስ
የህይወቴን ጎዳና ወደ ተስፋህ መልስ
በእምነቴም በኑሮ እንዲሁ አርጅቻለሁ
ዛሬ በአንተ መታደስን እሻለሁ

በሕይወት በኑሮ ጌታዬ ሆይ እጅግ ደክሜያለሁ
ፍሬ ሳይኖረኝ ዘመናትን ብዙ አሳልፌያለሁ
ሃይሌ አልቆብኝ ጉልበቶቼ እየተብረከረኩ
አለኝ ያልኩትን የያዝኩትን ከእጄ ተማረኩ

እኔ ባረጅ አታረጅም
ሽምግልና አንተን አያውቅ ህም
ሕይወቴን አንተ ታድሳለህ
ሸለቆዬን በውሃ ትሞላለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትኖራለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትሰራለህ

ሽምግልናዬን ጌታዬ ሆይ አድስ
የሕይወቴን ጎዳና ወደ ተስፋህ መልስ
በእምነቴም በኑሮ እንዲሁ አርጅቻለሁ
ዛሬ በአንተ መታደስን እሻለሁ

እምነቴ በፊትህ እጅግ ደክሞ ውስጤ ባዶ ሆኗል
ወደ አንተ የሚያራምደኝ ብርታቱ ጠፍሮኛል
የቀድሞውን ብርቱነቴን ዓይኔ ማየት ናፍቃ
ነፍሴ ጎብኘኝ ትልሃለች ፊትህ ተንበርክካ

እኔ ባረጅ አታረጅም
ሽምግልና አንተን አያውቅ ህም
ሕይወቴን አንተ ታድሳለህ
ሸለቆዬን በውሃ ትሞላለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትኖራለህ
ጥንትም ብርቱ ነህ
ዛሬም ብርቱ ነህ
ነገም ትሰራለህ

እምነቴ በፊትህ እጅግ ደክሞ ውስጤ ባዶ ሆኗል
ወደ አንተ የሚያራምደኝ ብርታቱ ጠፍሮኛል
የቀድሞውን ብርቱነቴን ዓይኔ ማየት ናፍቃ
ነፍሴ ጎብኘኝ ትልሃለች ፊትህ ተንበርክካ