ሃሌ ፡ ሃሌሉያ (Hale Hallelujah) - ኤዶም ፡ ልዑልሰገድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤዶም ፡ ልዑልሰገድ
(Edom Leulseged)

Edom Leulseged 1.jpg


(1)

አንተ ፡ ገናና
(Ante Genana)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤዶም ፡ ልዑልሰገድ ፡ አልበሞች
(Albums by Edom Leulseged)

አዝ፣ ሃሌ ፡ ሃሌሉያ
ማለት ፡ ነው ፡ የሚያረካኝ
እኔ ፡ ከዚህ ፡ በላይ
ሌላ ፡ ቃል ፡ አይበቃኝ (፪x)

ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ወዳጄ
ልልህ ፡ እወዳለሁ ፡ ባለችኝ ፡ ቋንቋዬ ፡ (አቅሜ)
ዓለም ፡ ሳይፈጠር ፡ ተመስግኖ ፡ ኖሯል
ዓለምም ፡ ተፈጥሮ ፡ እስካሁን ፡ ተመልኳል
ትልቁም ፡ ትንሹም ፡ ገናና ፡ ብሎታል
እኔም ፡ ደግሞ ፡ አሁን ፡ ያንኑ ፡ ልደጋግም

አዝ፣ ሃሌ ፡ ሃሌሉያ
ማለት ፡ ነው ፡ የሚያረካኝ
እኔ ፡ ከዚህ ፡ በላይ
ሌላ ፡ ቃል ፡ አይበቃኝ (፪x)

ፍልስፍና ፡ በዝቶ ፡ ዕውቀት ፡ ተከማችቶ
ጥበብ ፡ በጥበብ ፡ ላይ ፡ ሲታይ ፡ ተደርቦ
ቆም ፡ ብዬ ፡ አሰብኩት ፡ የፈጠረውን
ሁሉንም ፡ አዋቁ ፡ ብልህ ፡ መሆኑን

አዝ፣ ሃሌ ፡ ሃሌሉያ
ማለት ፡ ነው ፡ የሚያረካኝ
እኔ ፡ ከዚህ ፡ በላይ
ሌላ ፡ ቃል ፡ አይበቃኝ (፪x)

የሊቅ ፡ ዕውቀት ፡ ቀርቶ ፡ የረቀቀውን
መቼ ፡ ቀላል ፡ ሆነ ፡ የሰውስ ፡ ጥበብ?
ሁሉን ፡ ለፈጠረ ፡ ለዚህ ፡ ድንቅ ፡ ጌታ
ሃሌሉያ ፡ እንጂ ፡ ምን ፡ ሊባል ፡ ነው ፡ ታዲያ?


አዝ፣ ሃሌ ፡ ሃሌሉያ
ማለት ፡ ነው ፡ የሚያረካኝ
እኔ ፡ ከዚህ ፡ በላይ
ሌላ ፡ ቃል ፡ አይበቃኝ (፪x)



}}