ብልህ ፡ ሰው ፡ ነፍሱን ፡ ያድናል (Beleh Sew Nefsun Yadenal) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Lyrics.jpg


(4)

መንግሥተ ፡ ሰማይ
(Mengeste Semay)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፸ ፪ (1980)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 2:41
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሞት ፡ ሕይወት ፡ ይመረጣል
ብልህ ፡ ሰው ፡ ነፍሱን ፡ ያድናል
በስምህ ፡ ትዕዛዝ ፡ ስር ፡ ያድራል

በልቡ ፡ አንተን ፡ ፈላጊ
ስምህን ፡ ጠሪ ፡ ይባረካል
በኑሮ ፡ የሚያስቀድምህ
የደስታን ፡ ካባን ፡ ይደርባል
ከእርኩሰት ፡ ታርቀዋለህ
በልቡ ፡ ዙፋን ፡ ላይ ፡ ነግሰህ
ሰላምን ፡ በውስጡ ፡ አኑሮ
ይጓዛል ፡ ደስታን ፡ ጨምሮ

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሞት ፡ ሕይወት ፡ ይመረጣል
ብልህ ፡ ሰው ፡ ነፍሱን ፡ ያድናል
በስምህ ፡ ትዕዛዝ ፡ ስር ፡ ያድራል

ከኋለኛው ፡ ሃዘን ፡ ይልቅ
የአሁኑን ፡ ጉስቁልና ፡ መርጦ
ጊዜያዊውን ፡ ተድላ ፡ ንቆ
ነፍሱን ፡ ከሥጋው ፡ ያየ ፡ አብልጦ
ብልህ ፡ ነው ፡ ጠቢብ ፡ አዋቂ
የሰማይ ፡ ሃገር ፡ ዘላቂ
ዘለዓለም ፡ እረፍትን ፡ አይቷል
ለተስፋው ፡ ምድር ፡ ተመርጧል

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሞት ፡ ሕይወት ፡ ይመረጣል
ብልህ ፡ ሰው ፡ ነፍሱን ፡ ያድናል
በስምህ ፡ ትዕዛዝ ፡ ስር ፡ ያድራል

በለመለመ ፡ መስክ ፡ አድሮ
የጠራ ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ ጠጥቶ
በአምላኩ ፡ እንክብካቤ ፡ አድርጐ
መጓዙን ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ አጥላልቶ
ከስታለች ፡ ተርባ ፡ ነፍሱ
ታውኳል ፡ ሥጋ ፡ መንፈሱ
ይመለስ ፡ ሚወድ ፡ ይመለስ
ሳይወድቅ ፡ ጉልበቱ ፡ ሳይፈር

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሞት ፡ ሕይወት ፡ ይመረጣል
ብልህ ፡ ሰው ፡ ነፍሱን ፡ ያድናል
በስምህ ፡ ትዕዛዝ ፡ ስር ፡ ያድራል (፬x)