ጠፊዋን ፡ ዓለም (Tefiwan Alem) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Dereje Kebede Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

ስብስብ
(Collection)

ቁጥር (Track):

፲ ፱ (19)

ርዝመት (Len.): 2:55
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

አዝ፦ ጠፊዋን ፡ ዓለም ፡ ተለይቼ
ለዘለዓለም ፡ ተሰናብቼ
የሚሞተው ፡ ተለውጦ
የማይሞተውን ፡ ኢየሱስን ፡ ለብሶ (፪x)

ከጌታ ፡ ጋር ፡ ልኖር ፡ እናፍቃለሁ
ዓለምንና ፡ ሃሳቧን ፡ ትቻለሁ
ከላይ ፡ የሚመጣውን ፡ እጠብቃለሁ
በቅጽበት ፡ ወደእርሱ ፡ እነጠቃለሁ

አዝ፦ ጠፊዋን ፡ ዓለም ፡ ተለይቼ
ለዘለዓለም ፡ ተሰናብቼ
የሚሞተው ፡ ተለውጦ
የማይሞተውን ፡ ኢየሱስን ፡ ለብሶ (፪x)

በጉጉት ፡ ናፍቆት ፡ ፊቱን ፡ ሳይ
ኢየሱስን ፡ ሳገኝ ፡ በላይ ፡ በሰማይ
ፊቱን ፡ ስመለከት ፡ እምባዬን ፡ ሲያይ
እየዳሰሰ ፡ ዓይኔን ፡ ያብሳል

አዝ፦ ጠፊዋን ፡ ዓለም ፡ ተለይቼ
ለዘለዓለም ፡ ተሰናብቼ
የሚሞተው ፡ ተለውጦ
የማይሞተውን ፡ ኢየሱስን ፡ ለብሶ

ጌታ ፡ መምጣቱ ፡ ያሳውጃል
በደጅ ፡ እንደቆመ ፡ ሕይወቴም ፡ ያውቃል
ቀኑ ፡ እንደደረሰ ፡ ተረድጄ
ተጨማሪ ፡ ዘይት ፡ ልግዛ ፡ ተግቼ

አዝ፦ ጠፊዋን ፡ ዓለም ፡ ተለይቼ
ለዘለዓለም ፡ ተሰናብቼ
የሚሞተው ፡ ተለውጦ
የማይሞተውን ፡ ኢየሱስን ፡ ለብሶ (፪x)