From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አጭር ፡ ጊዜ ፡ አይደለም ፡ ለረጅም ፡ ዘመናት
በድካም ፡ በትግል ፡ ላያሌ ፡ ዓመታት
በመውደቅ ፡ መነሳት ፡ በውጊያ ፡ በጭንቀት
እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ አለፈ ፡ ያ ፡ እሳት (፫x)
አዝ፦ ዞር ፡ ብዬ ፡ ሳየው ፡ ያሳለፍኩትን
አባጣ ፡ ጐርባጣ ፡ ጉድጓድ ፡ ገደሉን
ማመን ፡ ይሳነኛል ፡ ኃይል ፡ ከየት ፡ አገኘው
ለካ ፡ ኤልሻዳዩ ፡ ጠብቆኝ ፡ ቆሜያለሁ
ሥሙን ፡ አከብራለሁ
መራራ ፡ አይታኘክ ፡ የመከራ ፡ እንጀራ
የብቸኝነት ፡ ቤት ፡ እኔው ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
እንቅልፌን ፡ አጥቼ ፡ ብዙ ፡ ለሊት ፡ አልፏል
ዛሬ ፡ ግን ፡ ታሪክ ፡ ነው ፡ ተረት ፡ ነው ፡ ይወራል (፫x)
አዝ፦ ዞር ፡ ብዬ ፡ ሳየው ፡ ያሳለፍኩትን
አባጣ ፡ ጐርባጣ ፡ ጉድጓድ ፡ ገደሉን
ማመን ፡ ይሳነኛል ፡ ኃይል ፡ ከየት ፡ አገኘው
ለካ ፡ ኤልሻዳዩ ፡ ጠብቆኝ ፡ ቆሜያለሁ
ሥሙን ፡ አከብራለሁ
የሕይወቴ ፡ ማብቂያ ፡ ዛሬ ፡ ነው ፡ ያልኩበት
ዓይኖቼን ፡ ጨፍኜ ፡ ሞትን ፡ ያሰብኩበት
ቀውጤው ፡ ሰዓት ፡ አልፎ ፡ ማየቴ ፡ ደንቆኛል
ለካ ፡ ጌታ ፡ ወዶኝ ፡ እጅ ፡ እግሬን ፡ ጠብቋል (፫x)
አዝ፦ ዞር ፡ ብዬ ፡ ሳየው ፡ ያሳለፍኩትን
አባጣ ፡ ጐርባጣ ፡ ጉድጓድ ፡ ገደሉን
ማመን ፡ ይሳነኛል ፡ ኃይል ፡ ከየት ፡ አገኘው
ለካ ፡ ኤልሻዳዩ ፡ ጠብቆኝ ፡ ቆሜያለሁ
ሥሙን ፡ አከብራለሁ (፪x)
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ በክንፉ ፡ ሸሸገኝ
ለካ ፡ መጐዳቴን ፡ ተጐሳቁዬ ፡ አየኝ
ያን ፡ ሁሉ ፡ ሻካራ ፡ ያን ፡ ሁሉ ፡ ጐርባጣ
ጌታ ፡ ብርታት ፡ ሆነኝ ፡ ችዬው ፡ እንድወጣ (፫x)
አዝ፦ ዞር ፡ ብዬ ፡ ሳየው ፡ ያሳለፍኩትን
አባጣ ፡ ጐርባጣ ፡ ጉድጓድ ፡ ገደሉን
ማመን ፡ ይሳነኛል ፡ ኃይል ፡ ከየት ፡ አገኘው
ለካ ፡ ኤልሻዳዩ ፡ ጠብቆኝ ፡ ቆሜያለሁ
ሥሙን ፡ አከብራለሁ
|