From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ደረጀ ፡ ከበደ (Dereje Kebede)
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
አዳኜ ፡ ኢኢየሱስ (Adagne Iyesus)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፳ ፻ ፪ (2010)
|
ቁጥር (Track):
|
፭ (5)
|
ርዝመት (Len.):
|
3:47
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች (Albums by Dereje Kebede)
|
|
የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ
ተቀናቃኝ ፡ የለው ፡ ወይም ፡ ባላጋራ
ፊት ፡ ለፊት ፡ የሚቆም ፡ ግጥሚያ ፡ ከርሱ ፡ ጋራ (፪x)
በአህዛብ ፡ ፊት ፡ ሊቀርብ ፡ በድንቅ ፡ ይገለጣል
ብንወድም ፡ ባንወድም ፡ ኢየሱስ ፡ ይነግሳል (፪x)
የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)
ከእንግዲህ ፡ ለውርደት ፡ ለሞት ፡ አይሰጥም
አንድ ፡ ጊዜ ፡ በመስቀል ፡ ፈጽሟል ፡ ሁሉንም (፪x)
ያነ ፡ እዳ ፡ ሊከፍል ፡ ዛሬ ፡ ዳኛ ፡ ሆኖ
ይመጣል ፡ ጌታችን ፡ በክብር ፡ ተክኖ (፪x)
የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)
ከዘመናት ፡ በፊት ፡ ሁሉን ፡ ጥለው ፡ ያሉ
ለርሱ ፡ የተገዙ ፡ ሞፈር ፡ ቀንበር ፡ ሳይሉ (፪x)
በታላቅ ፡ እልልታ ፡ በሆታ ፡ በደስታ
በአይናቸው ፡ ያዩታል ፡ የዘላለሙን ፡ ጌታ (፪x)
የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)
ከደመናው ፡ መሃል ፡ ግርማው ፡ የሚያስፈራ
በመላዕክት ፡ ታጅቦ ፡ ከአገልጋዮች ፡ ጋራ (፪x)
የቅዱሳን ፡ አባት ፡ ስሙም ፡ አማኑኤል
በከዋክብት ፡ ደምቆ ፡ አሜን ፡ ከተፍ ፡ ይላል (፪x)
የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)
|