የሚመጣ (Yemimeta) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Dereje Kebede Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

አዳኜ ፡ ኢኢየሱስ
(Adagne Iyesus)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 3:47
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ
ተቀናቃኝ ፡ የለው ፡ ወይም ፡ ባላጋራ
ፊት ፡ ለፊት ፡ የሚቆም ፡ ግጥሚያ ፡ ከርሱ ፡ ጋራ (፪x)
በአህዛብ ፡ ፊት ፡ ሊቀርብ ፡ በድንቅ ፡ ይገለጣል
ብንወድም ፡ ባንወድም ፡ ኢየሱስ ፡ ይነግሳል (፪x)

የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ከእንግዲህ ፡ ለውርደት ፡ ለሞት ፡ አይሰጥም
አንድ ፡ ጊዜ ፡ በመስቀል ፡ ፈጽሟል ፡ ሁሉንም (፪x)
ያነ ፡ እዳ ፡ ሊከፍል ፡ ዛሬ ፡ ዳኛ ፡ ሆኖ
ይመጣል ፡ ጌታችን ፡ በክብር ፡ ተክኖ (፪x)

የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ከዘመናት ፡ በፊት ፡ ሁሉን ፡ ጥለው ፡ ያሉ
ለርሱ ፡ የተገዙ ፡ ሞፈር ፡ ቀንበር ፡ ሳይሉ (፪x)
በታላቅ ፡ እልልታ ፡ በሆታ ፡ በደስታ
በአይናቸው ፡ ያዩታል ፡ የዘላለሙን ፡ ጌታ (፪x)

የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ከደመናው ፡ መሃል ፡ ግርማው ፡ የሚያስፈራ
በመላዕክት ፡ ታጅቦ ፡ ከአገልጋዮች ፡ ጋራ (፪x)
የቅዱሳን ፡ አባት ፡ ስሙም ፡ አማኑኤል
በከዋክብት ፡ ደምቆ ፡ አሜን ፡ ከተፍ ፡ ይላል (፪x)

የሚመጣ ፡ የሚከብር ፡ የሚነግስ ፡ ኢየሱስ (፪x)