Dereje Kebede/Adagnie Yesus/Adagnie Yesus

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ደረጀ ከበደ ርዕስ አዳኜ ኢየሱስ አልበም አዳኜ ኢየሱስ

አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት

ነፍሴን አስጨንቛት የጥላቴ ጩኸት አይኖቼን ባቀና ከላይ ስመለከት ከመቅደሱ ሆኖ እምባዬን አበሰ ያሰረኝ ገመድ ጌታ በጣጠሰ

አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት

የሞት ቀንበር ከቦኝ ያመፅ ፈሳሽ ዉጦኝ ሲኦል አፉን ከፍቶ ባጥንቴ አስቀርቶኝ ስሞታ ነገርኩኝ ላምላኬ ሳልሰለች እግዚአብሔር ተቆጣ ምድር ተናወጠች

አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት

ጠላቴን ሰበረ እንዳያንሰራራ ከቁጣው ጢስ ወጣ ፍምም ከሱ በራ ባእድ የረገጠኝ እንደመንገድ ጭቃ ነፃነቴን ሰጠኝ መቆዘሜ አበቃ

አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት እግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት

ዛሬማ ሰው ሆኜ ቀስት እገትራለሁ በኮረብታ ቆሜ ምሥጋና እሰዋለሁ ፅኑ እግር ለሰጠኝ የማይንሸራተት ለናዝሬቱ ኢየሱስ እጥፍ ልስገድለት

አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት