Dereje Kebede/Adagnie Yesus/Adagnie Yesus

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
  1. Numbered list item

ዘማሪ ደረጀ ከበደ

ርዕስ አዳኜ ኢየሱስ


አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ልቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት


ነፍሴን አስጨንቋት የጠላቴ ጩኸት አይኖቼን ባቀና ከላይ ስመለከት ከመቅደሱ ሆኖ እምባዬን አበሰ ያሰረኝን ገመድ ጌታ በጣጠሰ

 አዝ  

አዳኜ ኢየሱስ ገናናው

የሞት ቀንበር ከቦኝ ያመፅ ፈሳሽ ውጦኝ ሲኦል አፉን ከፍቶ ባጥንቴ አስቀርቶኝ ስሞታ ነገርኩኝ ላምላኬ ሳልሰለች እግዚአብሔር ተቆጣ ምድር ተናወጠች

አዝ አዳኜ ኢየሱስ

ጠላቴን ሰበረ እንዳያንሰራራ ከቁጣው ጢስ ወጣ ፍምም ከሱ በራ ባእድ የረገጠኝ እንደመንገድ ጭቃ ነፃነቴን ሰጠኝ መቆዘሜ አበቃ

አዝ አዳኜ ኢየሱስ

ዛሬማ ሰው ሆኜ ቀስት እገትራለሁ በኮረብታ ቆሜ ምሥጋና እሰዋለሁ ፅኑ እግር ለሰጠኝ የማይንሸራተት ለናዝሬቱ ኢየሱስ እጥፍ ልስገድለት

አዝ 

አዳኜ ኢየሱስ ገናናው