Dereje Kebede/Adagnie Yesus/Adagnie Yesus
ዘማሪ ደረጀ ከበደ ርዕስ አዳኜ ኢየሱስ አልበም አዳኜ ኢየሱስ
አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት
ነፍሴን አስጨንቛት የጥላቴ ጩኸት አይኖቼን ባቀና ከላይ ስመለከት ከመቅደሱ ሆኖ እምባዬን አበሰ ያሰረኝ ገመድ ጌታ በጣጠሰ
አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት
የሞት ቀንበር ከቦኝ ያመፅ ፈሳሽ ዉጦኝ ሲኦል አፉን ከፍቶ ባጥንቴ አስቀርቶኝ ስሞታ ነገርኩኝ ላምላኬ ሳልሰለች እግዚአብሔር ተቆጣ ምድር ተናወጠች
አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት
ጠላቴን ሰበረ እንዳያንሰራራ ከቁጣው ጢስ ወጣ ፍምም ከሱ በራ ባእድ የረገጠኝ እንደመንገድ ጭቃ ነፃነቴን ሰጠኝ መቆዘሜ አበቃ
አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት እግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት
ዛሬማ ሰው ሆኜ ቀስት እገትራለሁ በኮረብታ ቆሜ ምሥጋና እሰዋለሁ ፅኑ እግር ለሰጠኝ የማይንሸራተት ለናዝሬቱ ኢየሱስ እጥፍ ልስገድለት
አዝ አዳኜ ኢየሱስ ገናናው የእጄን ሰንሰለት በጠሰው ተመስገን ልበል ለቀኝለት በእግሩ ሥር ልውደቅ ልስገድለት ይህም አነሰበት