እጄን ይዞ (Ejien Yizo) - ዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ
(Dawit Wolde)

Dawit Wolde 1.jpeg


(1)

መዝሙር ፺ ፩
(Mezmur 91)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(9)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Wolde)

አንዳንዴ : ሳስታውስ : የአለም : ኑሮዬን
እንደተሰቃየሁ : ሳላገኝ : ጌታዬን
ሰላም : ስሻ : ስከንፍ : ስቀር : በየቦታው
ፈልጎ : አዳነኝ : የሰላሜ : ጌታ

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

የጭንቀት : ገደልን : ልወጣ : ስቧጥጥ
ወጥቼ : ወጥቼ : ተመልሼ : ስወድቅ
ልጁን : ላከ : ለኔ : መጠለያ : ሆነኝ
ከረግረጉ : ኃጢያት : ባህር : ወስጥ : አወጣኝ

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

ስሙን : ኢየሱስ : አሉት : አዳኝ : ስለሆነ
ኃጥአን : ሊድኑበት : እርሱ : መነመነ
እኔን : አሰቃዩኝ : እነርሱን : ተዉአቸው
ብሎ : እነ : ጴጥሮስን : ከጉድ : አዳናቸው

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

ሃሌሉያ : ሃሌሉያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ