From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ግርም ፡ ይለኛል (ይለኛል)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ይለኛል (፪x)
መልካም ፡ ነው (መልካም ፡ ነው)
መልካም ፡ ነው (፪x)
መንገድ ፡ ላይ ፡ ጥሎኝ ፡ አልሄደም
ደከመኝ ፡ ሰለቸኝ ፡ አላለም
እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው ፡ እላለሁ (፬x)
ቀንና ፡ ሌሊቱ ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ ይሉታል
መላዕክት ፡ ፍጥረቱ ፡ ሁሉ ፡ ያመልኩታል
አባቶች ፡ አምልከው ፡ አክብረውት ፡ አልፈዋል
በእኔና ፡ በቤቴ ፡ ጌታ ፡ ይመለካል
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ግርም ፡ ይለኛል (ይለኛል)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ይለኛል (፪x)
መልካም ፡ ነው (መልካም ፡ ነው)
መልካም ፡ ነው (፪x)
የወደቀን ፡ ይነሳል ፡ ያለው
የሳተውን ፡ የሚመልሰው
ኢየሱሴን ፡ እወደዋለሁ (፬x)
እንደሌዊ ፡ አይደል ፡ እንዴት ፡ ትቶኝ ፡ ያልፋል
ልክ ፡ እንደ ፡ ካህኑ ፡ መች ፡ ያፈገፍጋል
ደጉ ፡ ጌታ ፡ እየሱስ ፡ እጁን ፡ ይዘረጋል
ቁስሌን ፡ በዘይቱ ፡ ቀብቶ ፡ ያነሳኛል
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ግርም ፡ ይለኛል (ይለኛል)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ይለኛል (፪x)
መልካም ፡ ነው (መልካም ፡ ነው)
መልካም ፡ ነው (፪x)
ላቆም ፡ ነው ፡ አልሰግድም ፡ ብዬ
አልቀረሁም ፡ እሳት ፡ ዉስጥ ፡ ተጥዬ
ይታመናል ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ ጌታዬ (፬x)
ሰባት ፡ እጥፍ ፡ ሲነድ ፡ ወርውረው ፡ ጣሉኝ
የአማልክት ፡ አምላክ ፡ እዛው ፡ አገኘኝ
ኧረ ፡ እንዴት ፡ ተረፈ ፡ ከእሳት ፡ ያላችሁ
ከመከራው ፡ በፊት ፡ እየሱስ ፡ ያግኛቹ
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ግርም ፡ ይለኛል (ይለኛል)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ይለኛል (፪x)
መልካም ፡ ነው (መልካም ፡ ነው)
መልካም ፡ ነው (፪x)
|