እጠብቅሃለሁ (Etebeqehalehu) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 5:32
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ሰምቼ ፡ ነበረ ፡ ስታንኳኳ ፡ በሬን
ግን ፡ አላስተዋልኩም ፡ አንተ ፡ መሆንህን
ብዙ ፡ አድክሜሃለሁ ፡ አውቃልሁ ፡ እራሴ
ግን ፡ እራርተህልኝ ፡ ቤቴ ፡ ትመጣ ፡ ይሆን

አዝ:- እጠብቅሃለሁ ፡ ጌታ ፡ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ
በመጠበቂያዬ ፡ ላይ ፡ ዳግም ፡ እስክትመጣ
ድምፅህን ፡ አሰማኝ ፡ ልቤ ፡ እንዲፅናና
ግን ፡ አንተ ፡ ዝም ፡ ካልከኝ ፡ እፈራለሁና

ዝም ፡ ስትል ፡ ጊዜ ፡ ስታጠፋ ፡ ድምጽህን
ያሰብኩት ፡ በሙሉ ፡ እንዳልነበር ፡ ሲሆን
ቀኑ ፡ ሲጨላልም ፡ ፈርቼ ፡ ይህን ፡ ሁኔታ
መልዕክት ፡ ልኬ ፡ ነበር ፡ ትመጣ ፡ ይሆን ፡ የሚል

አዝ:- እጠብቅሃለሁ ፡ ጌታ ፡ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ
በመጠበቂያዬ ፡ ላይ ፡ ዳግም ፡ እስክትመጣ
ድምፅህን ፡ አሰማኝ ፡ ልቤ ፡ እንዲፅናና
ግን ፡ አንተ ፡ ዝም ፡ ካልከኝ ፡ እጠፋለሁና

እንግዳዬ ፡ ኢየሱስ ፡ እረፍ ፡ ቤቴ ፡ ገብተህ
ብዙ ፡ የምነግርህ ፡ አለኝ ፡ ማጫውትህ
ልቤ ፡ አንተ ፡ ቤት ፡ ነው ፡ ሀሳብህን ፡ ፈፅም
እጠብቅሃለሁ ፡ ከቶ ፡ አልሰለችም