ለእኔ ፡ ክብሬ (Lenie Kebrie) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 6.jpg


(6)

የሰው ፡ እጅ ፡ የሌለበት
(Yesew Ej Yelielebet)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

 
አዝእግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ለእኔ ፡ ክብሬ
ውበት ፡ ሞገስ ፡ ዘውድ ፡ አክሊሌ (፪x)
ከቶ ፡ የማይርቅ ፡ በፍፁም ፡ ከአጠገቤ
ሚራራልኝ ፡ ክብሬ ፡ ነው ፡ ጥጋቤ
አይጓደል ፡ በፍፁም ፡ ምሥጋናዉ
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ ይድመቅ ፡ ዕልልታው

በቅዱሳን ፡ ጉባኤ ፡ ህብረት ፡ መሃል
ሊመሰገን ፡ ሊከብር ፡ ይገባዋል
መልካም ፡ መዓዛ ፡ ሆኖ ፡ ያርግ ፡ መሥዋዕቴ
ለወደደኝ ፡ አፍቃሪ ፡ መድሃኒቴ

ይድመቅ ፡ ጭብጨባው ፡ ይድመቅ ፡ ዕልልታውም ፡ ይሰማ
ምሥጋና ፡ በአሪያም ፡ ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ነውና (፪x)

የአገኘሁት ፡ ደህንነት ፡ ለመንፈሴ
ዳግም ፡ ልደት ፡ በደሙ ፡ መቀደሴ
የአምላክ ፡ መንግሥት ፡ ወራሽ ፡ አድርጐኛል
ባመሰግን ፡ ብዘምር ፡ ያንስበታል

ሆ ፡ ትበል ፡ ዛሬ ፡ ነፍሴ
ታምጣ ፡ ለእርሱ ፡ ምሥጋና
ውዳሴ ፡ ለንጉሡ
ጌታ ፡ ድንቅ ፡ ነውና (፪x)

አዝእግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ለእኔ ፡ ክብሬ
ውበት ፡ ሞገስ ፡ ዘውድ ፡ አክሊሌ (፪x)
ከቶ ፡ የማይርቅ ፡ በፍፁም ፡ ከአጠገቤ
ሚራራልኝ ፡ ክብሬ ፡ ነው ፡ ጥጋቤ
አይጓደል ፡ በፍፁም ፡ ምሥጋናዉ
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ ይድመቅ ፡ ዕልልታው

ይዘምራል ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ ክብሬ ፡ እያለ
በአምላኩ ፡ ሰው ፡ መሆኑን ፡ ያስተዋለ
ሕይወት ፡ የለውም ፡ ከጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሌላ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ክርስቶስ ፡ የእርሱ ፡ ተድላ

ይድመቅ ፡ ጭብጨባው ፡ ይድመቅ ፡ ዕልልታውም ፡ ይሰማ
ምሥጋና ፡ በአሪያም ፡ ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ነውና (፪x)