ከምንጩ (Kemenchu) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 6.jpg


(6)

የሰው ፡ እጅ ፡ የሌለበት
(Yesew Ej Yelielebet)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ፦ ከምንጩ ፡ ስለቀዳሁ ፡ ስለጠጣሁ ፡ ስለረካች ፡ ነፍሴ
ምህረት ፡ ስላገኘሁ ፡ አቀርባለሁ ፡ ክብርና ፡ ውዳሴ
በደሙ ፡ ስለዋጀኝ ፡ ስላዳነኝ ፡ የዘለዓለም ፡ አምላክ
ለኪዳኑ ፡ ስላሰበኝ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ ጌታዬን ፡ ስባርክ

ላመስግነው ፡ ከፍ ፡ ይበል ፡ መድህኔ
ስላዳነኝ ፡ ከሞት ፡ ከኩነኔ
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ የጸዮኑ ፡ አለት
ተቆረጠ ፡ የኀጢአት ፡ ሰንሰለት

ለቤዛ ፡ ቀን ፡ በእርሱ ፡ ታትሜያለሁ
በመንፈሱ ፡ ልደት ፡ አግኝቻለሁ
ሠማያዊ ፡ ዜጋ ፡ የመንግሥቱ
ተመረጥኩኘ ፡ እንድኖር ፡ በእርስቱ

ፀጋ ፡ ሰጠኝ ፡ የዘለላእም ፡ ደህንነት
ታማኝ ፡ ጌታ ፡ ለተደገፉበት
ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በየእለቱ
ላገልግለው ፡ በደስታ ፡ በቤቱ

አዝ፦ ከምንጩ ፡ ስለቀዳሁ ፡ ስለጠጣሁ ፡ ስለረካች ፡ ነፍሴ
ምህረት ፡ ስላገኘሁ ፡ አቀርባለሁ ፡ ክብርና ፡ ውዳሴ
በደሙ ፡ ስለዋጀኝ ፡ ስላዳነኝ ፡ የዘለዓለም ፡ አምላክ
ለኪዳኑ ፡ ስላሰበኝ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ ጌታዬን ፡ ስባርክ

ላመስግነው ፡ ከፍ ፡ ይበል ፡ መድህኔ
ስላዳነኝ ፡ ከሞት ፡ ከኩነኔ
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ የጸዮኑ ፡ አለት
ተቆረጠ ፡ የኀጢአት ፡ ሰንሰለት

አምልኮዬ ፡ ለመድሃኒዓለም
ታላቅ ፡ ስሙ ፡ ይመስገን ፡ ዘለዓለም
ለሚገዛው ፡ ሠማይን ፡ ምድርን
አውጃለሁ ፡ ዘምራለሁ ፡ ክብሩን

ለታደገኝ ፡ ለታማኝ ፡ ወዳጄ
ዘምራለሁ ፡ በደስታ ፡ ፈቅጄ
አወራለሁ ፡ ፍቅሩን ፡ ተዐምራቱን
እርሱ ፡ ብቻ ፡ መድሃኒት ፡ መሆኑን

አይገርምም ፡ ወይ ፡ በአምላክ ፡ መታሰቤ
ላገለግል ፡ ለአመልከው ፡ ቀርቤ
የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ አገልጋይ ፡ በቤቱ
ሎሌ ፡ አደረገኝ ፡ ጌታ ፡ በችሎቱ

ኢየሱስ ፡ ይክበር ፡ ይድመቅ ፡ በሕይወቴ
እርሱ ፡ አይደል ፡ ወይ ፡ ስሬ ፡ መሰረቴ
ጠጥቻለሁ ፡ የዘለዓለም ፡ ውሃ
ለመለመ ፡ የነፍሴ ፡ በረሃ

አዝ፦ ከምንጩ ፡ ስለቀዳሁ ፡ ስለጠጣሁ ፡ ስለረካች ፡ ነፍሴ
ምህረት ፡ ስላገኘሁ ፡ አቀርባለሁ ፡ ክብርና ፡ ውዳሴ
በደሙ ፡ ስለዋጀኝ ፡ ስላዳነኝ ፡ የዘለዓለም ፡ አምላክ
ለኪዳኑ ፡ ስላሰበኝ ፡ ደስ ፡ ይለኛል ፡ ጌታዬን ፡ ስባርክ

ላመስግነው ፡ ከፍ ፡ ይበል ፡ መድህኔ
ስላዳነኝ ፡ ከሞት ፡ ከኩነኔ
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ የጸዮኑ ፡ አለት
ተቆረጠ ፡ የኀጢአት ፡ ሰንሰለት