ሃሌሉያ ፡ ልበል (Hallelujah Lebel) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 6.jpg


(6)

የሰው ፡ እጅ ፡ የሌለበት
(Yesew Ej Yelielebet)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(9)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ የሕይወቴ ፡ ጌታ ፡ ኦሆ
ጽኑ ፡ መሰረቴ ፡ የነፍሴ ፡ መከታ
የራራልኝ ፡ ቀድሞ ፡ በፍቅሩ ፡ የሳበኝ
ጨለማዬን ፡ ገፎጭ ፡ በብርሃን ፡ ያኖረኝ

ቅኔን ፡ ጨመረልኝ ፡ በአፌ
ለክብሩ ፡ እንድዘምር ፡ ከልቤ
ምሥጋናውን ፡ ደግሞ ፡ እንዳወራ
አብሬ ፡ እንዳመልከው ፡ ከቅዱሳን ፡ ጋራ
ከአሪያም ፡ ወረደ ፡ መንፈሱ
ልቤን ፡ አደረገው ፡ መቅደሱ
አቤት ፡ የአምላክ ፡ ፍቅር ፡ ምህረቱ
ኢኸው ፡ ልጅ ፡ አደረገኝ ፡ እንድኖር ፡ በቤቱ

ከቁጥር ፡ ያለፈ ፡ ቸርነት ፡ ሠማያዊ ፡ ፀጋን ፡ አሄ
አምላኬ ፡ ሰጥቶኛል ፡ የዘለዓለም ፡ ሕይወት
ማዳኑን ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ገለጠ
በደሙ ፡ ቀደሰኝ ፡ አሄ
ኢየሱስ ፡ ሕይወቴን ፡ መልካም ፡ አደረገ

ምድር ፡ እልል ፡ ትበል ፡ ለንጉሡ
ሠማይም ፡ ያጨብጭብ ፡ ለቅዱሱ
ሁሉንም ፡ በኃይሉ ፡ የፈጠረው
የዘለዓለም ፡ ዓለም ፡ መንግሥት ፡ የእግዚአብሔር ፡ ነው

ማዳኑን ፡ ልዘምር ፡ ከፍ ፡ ላድርገው
ከምርጦቹ ፡ ጋራ ፡ ላመስግነው
የጠለቀ ፡ ፍቅሩንም ፡ ልናገር
ከሠማይ ፡ በምድር ፡ ታላቅ ፡ ስሙ ፡ ይክበር

ፍቅሩን ፡ አፈሰሰ ፡ ማዳኑን ፡ ገለጠ ፡ እህ
በመስቀል ፡ ላይ ፡ ሞቶ ፡ ምህረቱን ፡ አወጀ
እርሱን ፡ ያመነች ፡ ነፍ ፡ በሕይወት ፡ ትኖር ፡ ዘንድ
ቤዛ ፡ ለዓለሙ ፡ ሆነ ፡ የኀጢአት ፡ መሥዋዕት

ሞትን ፡ ያሸነፈ ፡ ግድለኛ ፡ ማኅተሙን ፡ የፈታ ፡ ኃይለኛ
የነገሥታት ፡ ንጉሥ ፡ አንበሳ ፡ ምሥጋና ፡ የሚገባው ፡ ክብርና ፡ ሙገሳ
የጌቶቹ ፡ ጌታ ፡ ግርማዊ ፡ መንግሥት ፡ ከላይ ፡ ነው ፡ ሠማያዊ
ፍጥረት ፡ በመገዛት ፡ የሚያከብረው ፡ የዓለም ፡ መድሃኒት ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው

አቻ ፡ ይገኝለት ፡ መውደዱ ፡ አቤት ፡ የአምላክ ፡ ፍቅር ፡ አሄ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ምህረት ፡ ተገዝቶ ፡ አሄ
ምክሩ ፡ ከሰው ፡ ጥበብ ፡ የላቀ
ማስተዋሉ ፡ ረቂቅ ፡ አሄ
ይሄ ፡ ነው ፡ ጌታችን ፡ በክብር ፡ የደመቀ

ሃሌሉያ ፡ ልበል ፡ ላመስግነው
ኃይልና ፡ ጥበብም ፡ የእግዚአብሔር ፡ ነው
ሃሴት ፡ ታደርጋለች ፡ ዘወትር ፡ ነፍሴ
ሁሌ ፡ እያቀረበች ፡ ክብርና ፡ ውዳሴ

ክብር ፡ ለሚገባው ፡ ክብር ፡ ይሁን
በዙፋኑ ፡ ላለው ፡ ኦ ፡ ልዘምር
ለአማልክት ፡ አምላክ ፡ ይሁን ፡ ስግደት
በሠማይ ፡ በምድር ፡ ኃይልና ፡ በረከት

ሃሌሉያ ፡ ልበል ፡ ላመስግነው
ኃይልና ፡ ጥበብም ፡ የእግዚአብሔር ፡ ነው
ሃሴት ፡ ታደርጋለች ፡ ዘወትር ፡ ነፍሴ
ሁሌ ፡ እያቀረበች ፡ ክብርና ፡ ውዳሴ

ክብር ፡ ለሚገባው ፡ ክብር ፡ ይሁን
በዙፋኑ ፡ ላለው ፡ ኦ ፡ ልዘምር
ለአማልክት ፡ አምላክ ፡ ይሁን ፡ ስግደት
በሠማይ ፡ በምድር ፡ ኃይልና ፡ በረከት

"አምልኮና ፡ ስግደት ፡ ይሁንለት
አምልኮ ፡ ስግደት ፡ ይሁንለት
ለንጉሡ ፡ ለንጉሡ"