እኔማ (Eniema) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 4.jpg


(4)

ይሆናል
(Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2003)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 3:44
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝእኔማ ፡ እንዴት ፡ ላውራው
እንዴት ፡ ልተርከው ፡ ኦሆ
(፪x)
የአምላኬ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ስጦታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

ከእርሱ ፡ ጋር ፡ ስንጓዝ ፡ ባሳለፍኳቸው ፡ ዓመታት
ተለይቶኝ ፡ አያውቅም ፡ ለሰከንድ ፡ እንኳን ፡ ለሰዓት
ከእስትንፋሴ ፡ ይልቅ ፡ አምላኬ ፡ ለእኔ ፡ ቅርቤ ፡ ነው
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ ሁልጊዜ ፡ ለእኔ ፡ ታማኝ ፡ ነው

አዝእኔማ ፡ እንዴት ፡ ላውራው
እንዴት ፡ ልተርከው ፡ ኦሆ
(፪x)
የአምላኬ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ስጦታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

ሺህ ፡ ቃላቶች ፡ አይገልፁትም ፡ የጌታዬን ፡ ቸርነት
ምህረቱ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ልክ ፡ የለው ፡ ታማኝነቱ
ጥቂት ፡ አልቆጥብም ፡ ባለኝ ፡ ኃይሌ ፡ እዘምራለሁ
ክብር ፡ የኢየሱስ ፡ ነው ፡ ክብርን ፡ እሰጠዋለሁ

አዝእኔማ ፡ እንዴት ፡ ላውራው
እንዴት ፡ ልተርከው ፡ ኦሆ
(፪x)
የአምላኬ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ስጦታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

ጌታ ፡ አምላኬ ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ መኩራሪያ ፡ የምታመንበት
ኢየሱስ ፡ ብዬ ፡ ጠርቼው ፡ ምንጊዜም ፡ የማላፍርበት
ምህረቱን ፡ ልዘምር ፡ ፍቅሩን ፡ ደግሞ ፡ ተዓምራቱን
ሞገሱን ፡ በላዬ ፡ አፍሶታል ፡ በረከቱን

አዝእኔማ ፡ እንዴት ፡ ላውራው
እንዴት ፡ ልተርከው ፡ ኦሆ
(፪x)
የአምላኬ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ስጦታው ፡ ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው