ሰላም (Selam) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ:- ሰላም ፡ ነው ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ውሎ ፡ ማደር
መልካም ፡ አምላክ ፡ በእቅፉ ፡ ይዞኛል
አልሻም ፡ ምንም ፡ ከእርሱ ፡ ሌላ ፡ ወዳጅ ፡ የለም
ፍቅሩ ፡ ከጨለማ ፡ ስቦ ፡ አውጥቶኛል
ሁሉን ፡ በሚችለው ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አድራለሁ
ከክንፎቹ ፡ በታች ፡ እተማመናለሁ
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው (ኦሆሆሆ)
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው

ሰላምን ፡ ይሿታል ፡ በወርቅ ፡ በብር ፡ ሊያገኟት
በዓልማዝ ፡ በዕንቁ ፡ አትመጣም ፡ ምን ፡ ያህል ፡ ቢያፈሱላት
ከእግዚአብሔር ፡ የታረቀ ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ የዘየደ
በአምላክ ፡ ሰላም ፡ ይጠግባል ፡ በመንገዱ ፡ የሄደ (፪x)
በፈቃዱ ፡ የሄደ (፪x)

አዝ:- ሰላም ፡ ነው ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ውሎ ፡ ማደር
መልካም ፡ አምላክ ፡ በእቅፉ ፡ ይዞኛል
አልሻም ፡ ምንም ፡ ከእርሱ ፡ ሌላ ፡ ወዳጅ ፡ የለም
ፍቅሩ ፡ ከጨለማ ፡ ስቦ ፡ አውጥቶኛል
ሁሉን ፡ በሚችለው ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አድራለሁ
ከክንፎቹ ፡ በታች ፡ እተማመናለሁ
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው (ኦሆሆሆ)
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው

ሆድ ፡ በእንጀራ ፡ ቢሞላ ፡ ገላም ፡ ምርጡን ፡ ቢለብስ
የነፍስ ፡ ጐዶሎ ፡ አይሞላም ፡ ሰው ፡ ሁሉን ፡ ቢያግበሰብስ
ሰማያዊው ፡ ደስታ ፡ አምላክ ፡ ከላይ ፡ የላከው
ሰላም ፡ ማለት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ተሰፍሮ ፡ የማይለካው (፪x)

ሰው ፡ ዓለምን ፡ አትርፎ ፡ ውድ ፡ ነፍሱን ፡ ቢያዶላት
ከቶ ፡ ምን ፡ ይጠቅመዋል ፡ መጨረሻው ፡ ነው ፡ ጥፋት
ብሩክ ፡ ትሁን ፡ ያቺ ፡ ቀን ፡ ወንጌል ፡ የሰማሁባት
በክርስቶስ ፡ መስቀል ፡ ስራ ፡ ከአምላክ ፡ ጋር ፡ የታረቅኩባት (፪x)
ወንጌል ፡ የሰማሁባት ፡ አሄ ፡ ሰላም ፡ ያገኘሁባት

አዝ:- ሰላም ፡ ነው ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ውሎ ፡ ማደር
መልካም ፡ አምላክ ፡ በእቅፉ ፡ ይዞኛል
አልሻም ፡ ምንም ፡ ከእርሱ ፡ ሌላ ፡ ወዳጅ ፡ የለም
ፍቅሩ ፡ ከጨለማ ፡ ስቦ ፡ አውጥቶኛል
ሁሉን ፡ በሚችለው ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ አድራለሁ
ከክንፎቹ ፡ በታች ፡ እተማመናለሁ
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው (ኦሆሆሆ)
ጌታ ፡ መልካም ፡ አምላክ ፡ ነው