ክበርልኝ (Keberelegn) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

የድሃን ፡ ማድጋ ፡ ዘይት ፡ የሚሞላው
ከችግር ፡ አውጥቶ ፡ በደስታ ፡ ሚያኖረው
ለአንድ ፡ አይደለም ፡ ኢየሱስ ፡ ለብዙ ፡ ይተርፋል
ክበር ፡ እንበለው ፡ ይገባዋል

አዝ:- ክበር ፡ ክበርልን ፡ ክበር ፡ እንበለው
መክበር ፡ የሚገባው ፡ ቸር ፡ አምላክ ፡ ነው
ለቅሶን ፡ ወደ ፡ ደስታ ፡ ወደ ፡ ሳቅ ፡ ለውጧል
ኢየሱስ ፡ ሊመሰገን ፡ ይገባዋል

በሽባነት ፡ ታስሮ ፡ እንድሜውን ፡ ለፈጀው
ወዳጅ ፡ ዘመድ ፡ ትቶት ፡ ተስፋ ፡ ለቆረጠው
ታምረኛው ፡ ኢየሱስ ፡ በጊዜው ፡ ይደርሳል
እስራቱን ፡ ፈቶ ፡ ያዘልላል

አዝ:- ክበር ፡ ክበርልን ፡ ክበር ፡ እንበለው
መክበር ፡ የሚገባው ፡ ቸር ፡ አምላክ ፡ ነው
ለቅሶን ፡ ወደ ፡ ደስታ ፡ ወደ ፡ ሳቅ ፡ ለውጧል
ኢየሱስ ፡ ሊመሰገን ፡ ይገባዋል

ሙቱን ፡ ከመቃብር ፡ ተጣርቶ ፡ ያስነሳል
በቃ ፡ የተባለውን ፡ ነፍስ ፡ ይዘራበታል
ለእርሱ ፡ ማይታዘዝ ፡ ምን ፡ አለ ፡ በውኑ
ከፍ ፡ ብሎ ፡ ይንገሥ ፡ በዙፋኑ

አዝ:- ክበር ፡ ክበርልን ፡ ክበር ፡ እንበለው
መክበር ፡ የሚገባው ፡ ቸር ፡ አምላክ ፡ ነው
ለቅሶን ፡ ወደ ፡ ደስታ ፡ ወደ ፡ ሳቅ ፡ ለውጧል
ኢየሱስ ፡ ሊመሰገን ፡ ይገባዋል