በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል (Beante Des Yelegnal) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ:- አሁንማ ፤ ብርሃንህ ፡ በእኔ ፡ ደምቋል
መከራም ፡ ከኔ ፡ ርቋል ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ምን ፡ እላለሁ ፤ ስምክን ፡ ከማክበር ፡ በቀር ፡
ምን ፡ ልበል ፡ ምን ፡ ልናገር ፡ ስላደረክልኝ ፡ ነገር (፪x)

በዓለም ፡ ላይ ፡ ከሚታየው ፡ ከአልማዝ ፡ ከወርቅ ፡ ከዕንቁ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ይበልጣል ፡ አባት ፡ ነህ ፡ ለተጠቁ
ምስክር ፡ ነኝ ፡ ለዚህ ፡ እኔ ፡ ማዳንህን ፡ አይቻለሁ
ያባትነት ፡ ፍቅርህን ፡ ምህረትህን ፡ እዘምራለሁ

ተመስገን ፡ እያልኩ ፡ ላክብር ፡ ስምህን
በእርግጥ ፡ ስላየሁ ፡ ጌትነትህን
በአማረ ፡ ዜማ ፡ ቅኔ ፡ ውዳሴ
ልዑል ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ያክብርህ ፡ ነፍሴ

አዝ:- አሁንማ ፤ ብርሃንህ ፡ በእኔ ፡ ደምቋል
መከራም ፡ ከኔ ፡ ርቋል ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ምን ፡ እላለሁ ፤ ስምክን ፡ ከማክበር ፡ በቀር ፡
ምን ፡ ልበል ፡ ምን ፡ ልናገር ፡ ስላደረክልኝ ፡ ነገር (፪x)

ማረፊያ ፡ ለምስኪኑ ፡ ማጠጊያ ፡ ለደሃው ፡ ሰው
ይህንን ፡ አይቻለሁ ፡ እንባውን ፡ ስታብሰው
ደግ ፡ ነህ ፡ እግዚአብሔር ፡ መልካም ፡ ግሩም ፡ በምክርህ
ምህረትህ ፡ አይለካም ፡ ወደር ፡ የለው ፡ ለፍቅርህ

አሉ ፡ ብዙዎች ፡ የታደጋቸው
ስምህን ፡ የሚጠሩ ፡ በምሥጋናቸው
እያደነቁ ፡ ግሩም ፡ ስምህን
ይዘምራሉ ፡ ጌትነትህን

አዝ:- አሁንማ ፤ ብርሃንህ ፡ በእኔ ፡ ደምቋል
መከራም ፡ ከኔ ፡ ርቋል ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ምን ፡ እላለሁ ፤ ስምክን ፡ ከማክበር ፡ በቀር ፡
ምን ፡ ልበል ፡ ምን ፡ ልናገር ፡ ስላደረክልኝ ፡ ነገር (፪x)