አንበሳው (Anbesaw) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ:- ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው
አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x)
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው
ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው
ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል
ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x)

ያለፈው ፡ ታሪኬ ፡ አፍ ፡ አለው ፡ ያወራል
የጌታን ፡ ምህረት ፡ ፍቅር ፡ ይዘክራል
ያልተደረገልኝ ፡ ያልሆነ ፡ ምን ፡ አለ
የአምላኬ ፡ ምህረት ፡ በእኔ ፡ ገነነ
ያልተደረገልኝ ፡ ያልሆነ ፡ ምን ፡ አለ
የጌታ ፡ ምህረት ፡ በእኔ ፡ ገነነ

ይረዳል ፡ እኮ ፡ ከማንም ፡ በላይ
ተገርሜያለሁ ፡ ተአምራቱን ፡ ሳይ
ምስክሩ፡ ነኝ ፡ ሕያው ፡ ምልክቱ
ማዳኑን ፡ ያየሁ ፡ ሁሉን ፡ ቻይነቱን (፪x)

አዝ:- ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው
አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x)
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው
ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው
ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል
ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x)

ምህረቱን ፡ እውነቱን ፡ ፍቅሩን ፡ አስብና
የከበረ ፡ ስሙን ፡ አሞጋግስና
ሳመልከው ፡ ሳከብረው ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
እንደ ፡ ኢየሱስ/ጌታ ፡ ከየት ፡ ይገኛል (፪x)

ልዘምር ፡ ድንቁን ፡ በምክሩ ፡ ስቦኛል
አምላክ ፡ ለክብሩ ፡ በስሜ ፡ ጠርቶኛል
ያስደስተኛል ፡ የጌታ ፡ መሆኔ
ምህረት ፡ አገኘሁ ፡ ዳንኩኝ ፡ ከኩነኔ (፪x)

አዝ:- ከሁሉም ፡ የሚበልጥብኝ ፡ በማንም ፡ የማለውጠው
አንበሳው ፡ የጀግኖች ፡ ጀግና ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፪x)
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው
ፍቅሩ ፡ ግሩም ፡ እጁ ፡ ሰፊ ፡ ነው
ምንተስኖት ፡ ምን ፡ ያሳጣኛል
ቸርነቱን ፡ አብዝቶልኛል (፪x)