From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ:- አምላኬ ፡ ፍቅርህን ፡ ልንገር ፡ ምሥጋናህን (፪x)
እንከን ፡ የሌለብህ ፡ አባት ፡ መሆንህን (፪x)
በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ ያለበስከኝ ፡ ጸጋህ (፪x)
ሁሌ ፡ ያዘምረኛል ፡ አኑሮኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)
በስምህ ፡ አምኜ ፡ ልጅህ ፡ በመሆኔ
ሁልጊዜ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁኝ ፡ እኔ (፪x)
በዜማ ፡ በቅኔ ፡ ስምክን ፡ አውጃለሁ
ብዬ ፡ እየዘመርኩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው (፪x)
ገብተህ ፡ ከመንደሬ ፡ ከተደበቅኩበት
ፍቅርህ ፡ ልቤን ፡ ገዛው ፡ እጄን ፡ የያዝክበት
የሕይወትን ፡ ትርጉም ፡ የመኖርን ፡ ሚስጥር
ገልጠህ ፡ አሳየኸኝ ፡ በመስቀልህ ፡ ፍቅር
ምህረትህን ፡ አሳየኸኝ ፡ አሳየኸኝ ፡ ይቅርታ
ሰላምን ፡ ሰጥተኸኛል ፡ አቻ ፡ የለህ ፡ ኢየሱስ ፡ የኔ ፡ ጌታ
ልዘምር ፡ በደስታ ፡ ከእንግዲህ ፡ ምን ፡ እላለሁ
እግዚአብሔር ፡ ከወደደኝ ፡ ዝቅ ፡ ብዬ ፡ አመሰግናለሁ
የትንሳዔው ፡ ንጉሥ ፡ የትንሳዔው ፡ ጌታ
ኢየሱስ ፡ የኔ ፡ ወዳጅ ፡ የሕይወቴ ፡ አለኝታ
የሕይወት ፡ ውኃ ነህ ፡ ጥሜን ፡ አርክተሃል
በረሃው ፡ ሕይወቴን ፡ አለምልመኸዋል
ደህንነት ፡ አግኝቻለሁ ፡ ዕዳዬ ፡ ተሰርዟል
ኩነኔ ፡ በእኔ ፡ የለም ፡ አቤት ፡ ፍቅርህ ፡ ይህንን ፡ አድርጓል
ክብር ፡ ለስምህ ፡ ይሁን ፡ ተትረፍርፏል ፡ ሰላሜ
በደስታ ፡ ላምልክህ ፡ ላመስግንህ ፡ ደግሜ ፡ ደግሜ
አዝ:- አምላኬ ፡ ፍቅርህን ፡ ልንገር ፡ ምሥጋናህን (፪x)
እንከን ፡ የሌለብህ ፡ አባት ፡ መሆንህን (፪x)
በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ ያለበስከኝ ፡ ጸጋህ (፪x)
ሁሌ ፡ ያዘምረኛል ፡ አኑሮኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)
በስምህ ፡ አምኜ ፡ ልጅህ ፡ በመሆኔ
ሁልጊዜ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁኝ ፡ እኔ (፪x)
በዜማ ፡ በቅኔ ፡ ስምክን ፡ አውጃለሁ
ብዬ ፡ እየዘመርኩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው (፪x)
ዛሬ ፡ ሰው ፡ መሆኔን ፡ ሳስብ ፡ ይገርመኛል
በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ የአንተ ፡ አድርገኸኛል
መዳኔስ ፡ ብቻውን ፡ ተዐምር ፡ አይደለም ፡ ወይ
በአንተ ፡ መመረጤስ ፡ ብርሃንን ፡ እንዳይ
ለአምልክህ ፡ ተሰጥቼ ፡ በሙሉ ፡ ልቤ ፡ ልቀኝ
ቃልህን ፡ ላሰላስለው ፡ በእውነት ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ እንዳስተማርከኝ
ቅንነት ፡ ልቤን ፡ ይውረስ ፡ ልኑር ፡ እንደምትወደው
አምልኮዬ ፡ ንጹህ ፡ ይሁን ፡ ምሥጋናዬም ፡ አንተ ፡ ምታሸተው (፪x)
|