Daniel Amdemichael/Selam/Amlakie Feqrehen
| Artist vo 5 = Daniel Amdemichael | አምላኬ ፡ ፍቅርህን ፡ ልንገር ፡ ምሥጋናህን (፪x)
- እንከን ፡ የሌለብህ ፡ አባት ፡ መሆንህን (፪x)
- በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ ያለበስከኝ ፡ ጸጋህ (፪x)
- ሁሌ ፡ ያዘምረኛል ፡ አኑሮኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)
- በስምህ ፡ አምኜ ፡ ልጅህ ፡ በመሆኔ
- ሁልጊዜ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁኝ ፡ እኔ (፪x)
- በዜማ ፡ በቅኔ ፡ ስምክን ፡ አውጃለሁ
- ብዬ ፡ እየዘመርኩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው (፪x)
ገብተህ ፡ ከመንደሬ ፡ ከተደበቅኩበት ፍቅርህ ፡ ልቤን ፡ ገዛው ፡ እጄን ፡ የያዝክበት የሕይወትን ፡ ትርጉም ፡ የመኖርን ፡ ሚስጥር ገልጠህ ፡ አሳየኸኝ ፡ በመስቀልህ ፡ ፍቅር ምህረትህን ፡ አሳየኸኝ ፡ አሳየኸኝ ፡ ይቅርታ ሰላምን ፡ ሰጥተኸኛል ፡ አቻ ፡ የለህ ፡ ኢየሱስ ፡ የኔ ፡ ጌታ ልዘምር ፡ በደስታ ፡ ከእንግዲህ ፡ ምን ፡ እላለሁ እግዚአብሔር ፡ ከወደደኝ ፡ ዝቅ ፡ ብዬ ፡ አመሰግናለሁ
የትንሳዔው ፡ ንጉሥ ፡ የትንሳዔው ፡ ጌታ ኢየሱስ ፡ የኔ ፡ ወዳጅ ፡ የሕይወቴ ፡ አለኝታ የሕይወት ፡ ውኃ ነህ ፡ ጥሜን ፡ አርክተሃል በረሃው ፡ ሕይወቴን ፡ አለምልመኸዋል ደህንነት ፡ አግኝቻለሁ ፡ ዕዳዬ ፡ ተሰርዟል ኩነኔ ፡ በእኔ ፡ የለም ፡ አቤት ፡ ፍቅርህ ፡ ይህንን ፡ አድርጓል ክብር ፡ ለስምህ ፡ ይሁን ፡ ተትረፍርፏል ፡ ሰላሜ በደስታ ፡ ላምልክህ ፡ ላመስግንህ ፡ ደግሜ ፡ ደግሜ
- አዝ:- አምላኬ ፡ ፍቅርህን ፡ ልንገር ፡ ምሥጋናህን (፪x)
- እንከን ፡ የሌለብህ ፡ አባት ፡ መሆንህን (፪x)
- በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ ያለበስከኝ ፡ ጸጋህ (፪x)
- ሁሌ ፡ ያዘምረኛል ፡ አኑሮኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)
- በስምህ ፡ አምኜ ፡ ልጅህ ፡ በመሆኔ
- ሁልጊዜ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁኝ ፡ እኔ (፪x)
- በዜማ ፡ በቅኔ ፡ ስምክን ፡ አውጃለሁ
- ብዬ ፡ እየዘመርኩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው (፪x)
ዛሬ ፡ ሰው ፡ መሆኔን ፡ ሳስብ ፡ ይገርመኛል በደምህ ፡ ቀድሰህ ፡ የአንተ ፡ አድርገኸኛል መዳኔስ ፡ ብቻውን ፡ ተዐምር ፡ አይደለም ፡ ወይ በአንተ ፡ መመረጤስ ፡ ብርሃንን ፡ እንዳይ
ለአምልክህ ፡ ተሰጥቼ ፡ በሙሉ ፡ ልቤ ፡ ልቀኝ ቃልህን ፡ ላሰላስለው ፡ በእውነት ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ እንዳስተማርከኝ ቅንነት ፡ ልቤን ፡ ይውረስ ፡ ልኑር ፡ እንደምትወደው አምልኮዬ ፡ ንጹህ ፡ ይሁን ፡ ምሥጋናዬም ፡ አንተ ፡ ምታሸተው (፪x) </poem> }}