Daniel Amdemichael/Mognenet Hono Aydelem/Mech Eresahu

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


አዝ መች እረሳሁ መች ዘነጋሁ ሁሉንም አስታውሳለሁ ከሕጻንነቴ ጀምሮ ስትመራኝ ማዳንህን አይቻለሁ እጆቼን ላንሳ ላክብርህ ምሥጋናዬን ተቀበለው ብቻውን ተዓምር የሚያደርግ የሚሠራ ኧረ እንዳንተ ያለ ማነው? /3/

የራራልኝ በድካሜ ኃይል የሆነልኝ አቅሜ ጐኔ ቆሞ ያበረታኝ ማን ነበረ ከአንተ በላይ?

አዝ መች እረሳሁ መች ዘነጋሁ ሁሉንም አስታውሳለሁ ከሕጻንነቴ ጀምሮ ስትመራኝ ማዳንህን አይቻለሁ እጆቼን ላንሳ ላክብርህ ምሥጋናዬን ተቀበለው ብቻውን ተዓምር የሚያደርግ የሚሠራ ኧረ እንዳንተ ያለ ማነው? /3/

ከንፈሮቼን ቀባሃቸው ጠላቶቼ እያየ ዓይናቸው ዝማሬን በአፌ ጨምረሃል አመልክህ ዘንድ ይገባኛል

አዝ መች እረሳሁ መች ዘነጋሁ ሁሉንም አስታውሳለሁ ከሕጻንነቴ ጀምሮ ስትመራኝ ማዳንህን አይቻለሁ እጆቼን ላንሳ ላክብርህ ምሥጋናዬን ተቀበለው ብቻውን ተዓምር የሚያደርግ የሚሠራ ኧረ እንዳንተ ያለ ማነው? /3/

ሁሉም አልፎ እዚህ መድረሴ በአንተ እንጂ መች በራሴ ክብር ለአንተ እሰጣለሁ ሁልጊዜ እዘምራለሁ

አዝ መች እረሳሁ መች ዘነጋሁ ሁሉንም አስታውሳለሁ ከሕጻንነቴ ጀምሮ ስትመራኝ ማዳንህን አይቻለሁ እጆቼን ላንሳ ላክብርህ ምሥጋናዬን ተቀበለው ብቻውን ተዓምር የሚያደርግ የሚሠራ ኧረ እንዳንተ ያለ ማነው? /3/

ኸረ ይህን ኢየሱስ ምን ብዬ ልባርከው ውለታው በዛብኝ ከአይምሮዬ  በላይ ነው አቤት  ምህረቱ  ምን እከፍለዋለው እኔም ክብር አግንቼ  አገልጋይ ሆኛለሁ ይኸው ይድረስልኝ ዛሬ ምስጋናዬ ማለት ችያለውኝ  እኔም  አባ ብዬ

ሥራዬን የሠራህልኝ መንገዴን ያቀናህልኝ (፪x) አማኑኤል ከፍ በልልኝ (፫x) ኢየሱሴ ከፍ በልልኝ የእኔ ጌታ ከፍ በልልኝ

ተራራውን ንዶ ሜዳ ከአደረገው መራመድ ብቻ ነው ከእኔ ሚጠበቀው (፪x)

ጐዳናዬ ቀንቶ ተራመድ ብሎኛል ከእኔ ጋር ስላለ ማን ይቃወመኛል (፪x)

ማን ይቃወመኛል (፪x) የቱ ይይዘኛል (፪x)

አልፈራም ልቤ አይሰጋ ጌታዬ አለ ከእኔ ጋ አልፈራም ልቤ አይሰጋ የጠራኝ አለ ከእኔ ጋ አይቆምም ምንም ከፊቴ እግዚአብሔር ነው ዛሬም ጉልበቴ (፭x)


ልቤን ፍፁም ደስታ ሞላው የአንተ መሆኔን ሳስበው ብዙ ሰላም በዝቶልኛል ከአንተ እጅ ማን ያወጣኛል?

አዝ መች እረሳሁ መች ዘነጋሁ ሁሉንም አስታውሳለሁ ከሕጻንነቴ ጀምሮ ስትመራኝ ማዳንህን አይቻለሁ እጆቼን ላንሳ ላክብርህ ምሥጋናዬን ተቀበለው ብቻውን ተዓምር የሚያደርግ የሚሠራ ኧረ እንዳንተ ያለ ማነው? /3/