የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን (Yante Feqer Gen) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤልvolume =4

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤልvolume =4
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 1.jpg


(1)

አንበሳ
(Anbesa)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፰ (1996)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 5:51
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤልvolume =4 ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ፦ ድንጋዩ ፡ ልቤ ፡ ጠጣሩ ፡ ልቤ
መች ፡ በቀላሉ ፡ ታዛዥ ፡ ነበረ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን ፡ ውስጤን ፡ ሰበረ
ተረትቻለሁ ፡ ተሸንፌያለሁ
እየሱሴ ፡ ለአንተ ፡ እጅ ፡ ሰጥቻለሁ
ዛሬ ፡ በፍቅርህ ፡ ተማርኬያለሁ (፪x)

ብዙ ፡ የከበሩ ፡ በምድር ፡ ላይ ፡ ሞልተው
ታላቅ ፡ ነኝ ፡ ባዩን ፡ ልታሳፍረው
እኔን ፡ መረጥከኝ ፡ ዓሣ ፡ አጥማጁን ፡ ሰው
ኧረ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ኢየሱሴ ፡ ፍቅርህ
ሀብታም: ደሀ ፡ አይል ፡ አመራረጥህ
ለእኔም ፡ ደረሰኝ ፡ ድንቅ ፡ ማዳንህ

አዝ፦ ድንጋዩ ፡ ልቤ ፡ ጠጣሩ ፡ ልቤ
መች ፡ በቀላሉ ፡ ታዛዥ ፡ ነበረ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን ፡ ውስጤን ፡ ሰበረ
ተረትቻለሁ ፡ ተሸንፌያለሁ
እየሱሴ ፡ ለአንተ ፡ እጅ ፡ ሰጥቻለሁ

ዛሬ ፡ በፍቅርህ ፡ ተማርኬያለሁ

መች: ያልቃል፡ ጥረቴ ፡ ለዚህ ፡ ሥጋዬ
ቀን ፡ ከሌት፡ ስደክም ፡ መረቤን ፡ ጥዬ
ምንም ፡ ላላገኝ ፡ በድካም ፡ ዝዬ
አንተ ፡ ግን ፡ መጥተህ ፡ ተዓምርን ፡ ሰራህ
መላው ፡ ሕይወቴን ፡ መገረም ፡ ሞላ
ሥሜን ፡ ተግባሬን ፡ ኑሮዬን ፡ ቀየርክ

አዝ፦ ድንጋዩ ፡ ልቤ ፡ ጠጣሩ ፡ ልቤ
መች ፡ በቀላሉ ፡ ታዛዥ ፡ ነበረ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን ፡ ውስጤን ፡ ሰበረ
ተረትቻለሁ ፡ ተሸንፌያለሁ
እየሱሴ ፡ ለአንተ ፡ እጅ ፡ ሰጥቻለሁ
ዛሬ ፡ በፍቅርህ ፡ ተማርኬያለሁ

ከኋላዬ ፡ ና ፡ ወድጄሃልሁ
ለማዳን ፡ ሥራ ፡ መርጬሃልሁ
ሰዎችን ፡ አጥማጅ ፡ አደርግሃልሁ
ኣለኝ፡ ጌታዬ ፡ እኔም ፡ ተረታሁ
ከልብ ፡ ወደድኩህ ፡ ሕይወቴን ፡ ሰጠሁ
እስከ ፡ ዘለዓለም ፡ አመልክሃለሁ

አዝ፦ ድንጋዩ ፡ ልቤ ፡ ጠጣሩ ፡ ልቤ
መች ፡ በቀላሉ ፡ ታዛዥ ፡ ነበረ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን ፡ ውስጤን ፡ ሰበረ
ተረትቻለሁ ፡ ተሸንፌያለሁ
እየሱሴ ፡ ለአንተ ፡ እጅ ፡ ሰጥቻለሁ
ዛሬ ፡ በፍቅርህ ፡ ተማርኬያለሁ

የዋህነትህ፡ ትህትናህ ፡ ነው: የሳበኝ
በኃይል ፡ በጉልበት ፡ አላስገደድከኝ
ድንቅ ፡ ፍቅርህ ፡ ነው ፡ ያንበረከከኝ
ልከተል ፡ ወሰንኩ ፡ ከልብ ፡ ጌታዬ
በነገር ፡ ሁሉ ፡ አንተን ፡ ታምኜ
መረብ ፡ ታንኳዬን ፡ ሁሉንም ፡ ጥዬ

አዝ፦ ድንጋዩ ፡ ልቤ ፡ ጠጣሩ ፡ ልቤ
መች ፡ በቀላሉ ፡ ታዛዥ ፡ ነበረ
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ ግን ፡ ውስጤን ፡ ሰበረ
ተረትቻለሁ ፡ ተሸንፌያለሁ
እየሱሴ ፡ ለአንተ ፡ እጅ ፡ ሰጥቻለሁ
ዛሬ ፡ በፍቅርህ ፡ ተማርኬያለሁ (፪x)