ከወደድከው (Kewededkew) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 1.jpg


(1)

አንበሳ
(Anbesa)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፰ (1996)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 4:44
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ፦ከወደድከው ፡ ምሥጋናዬን ፡ ጌታ ፡ ከተቀበልከው
እሰዋለሁ ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታዬ ፡ አልሰለችም (፪x)

ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ከሚሉት ፡ እልፍ ፡ አላፍት ፡ መላዕክቶች
እኔንም ፡ ከደመርከኝ ፡ ከቤትህ ፡ ተቀኚዎች
መስዋዕቴን ፡ ከወደድከው ፡ ደስ ፡ ከተሰኸኘህበት
ይኸው ፡ ዝማሬ ፡ ኢየሱስ ፡ አንተው ፡ ከፍ ፡ በልበት

አዝ፦ከወደድከው ፡ ምሥጋናዬን ፡ ጌታ ፡ ከተቀበልከው
እሰዋለሁ ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታዬ ፡ አልሰለችም (፪x)

ጠቢባን ፡ አዋቂዎች ፡ በምድር ፡ ሞልተው ፡ እያሉ
ጥሪ ፡ አልደረሳቸውም ፡ ለዚህ ፡ ክብር ፡ አልታደሉም
ታላላቆቹን ፡ ንቀህ ፡ ምስኪኑን ፡ ታከብረዋለህ
ኧረ ፡ ተባረክ ፡ ኢየሱስ ፡ ፊት ፡ አይተህ ፡ መቼ ፡ ታደላለህ

አዝ፦ከወደድከው ፡ ምሥጋናዬን ፡ ጌታ ፡ ከተቀበልከው
እሰዋለሁ ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታዬ ፡ አልሰለችም (፪x)

ጠዋትም ፡ ማታም ፡ በአፌም ፡ ምሥጋናን ፡ እሰዋለሁ
የተቀደሰውን ፡ ሥምህን ፡ አከብራለሁ
ብቁ ፡ ሆኜ ፡ አይደለም ፡ ለዚህ ፡ የተገባሁኝ
ጌታ ፡ በምህረትህ ፡ ነው ፡ አንተው ፡ ይሁን ፡ ስላልከኝ

አዝ፦ከወደድከው ፡ ምሥጋናዬን ፡ ጌታ ፡ ከተቀበልከው
እሰዋለሁ ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታዬ ፡ አልሰለችም (፪x)

በህፃናት ፡ አፍም ፡ ምሥጋናን ፡ ታኖራለህ
የምስኪኑን ፡ አንደበት ፡ ዝማሬን ፡ ትሞላለህ
ይሁን ፡ አንተ ፡ ከፈቀድከው ፡ ይህንን ፡ ከወደድከው
እኔማ ፡ አይሰለቸኝም ፡ ጠዋት ፡ ማታ ፡ አዜማለሁ

አዝ፦ከወደድከው ፡ ምሥጋናዬን ፡ ጌታ ፡ ከተቀበልከው
እሰዋለሁ ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታዬ ፡ አልሰለችም (፪x)