ችላ ፡ አትበል (Chela Atebel) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 1.jpg


(1)

አንበሳ
(Anbesa)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፰ (1996)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 4:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ፦ ኧረ ፡ ተው ፡ ወንድሜ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበል
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተል
ኧረ ፡ ተይ ፡ እህቴ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበይ
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተይ

አያዋጣም ፡ እዚም ፡ እዚያም
መረጋገጥ ፡ እንዲያው ፡ መዋተት
ትርፉ ፡ ሞት ፡ ነው ፡ ተው ፡ ወንድሜ
አያዛልቅ ፡ በኃጢአት ፡ መዋኘት

ወስነህ ፡ ተቀበል ፡ ጌታን ፡ በልብህ
ኃጢአት ፡ አያባብለህ ፡ ጨክነህ ፡ ተወው ፡ ተወው ፡ ይቅርብህ

አዝ፦ ኧረ ፡ ተው ፡ ወንድሜ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበል
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተል
ኧረ ፡ ተይ ፡ እህቴ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበይ
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተይ

የዓለም ፡ ኑሮ ፡ እሽኮለሌው
እያሳሳቀ ፡ ወደ ፡ ሞት ፡ ነው
ይልቅ ፡ ንቃ ፡ ዛሬ ፡ ወስን
ሞት ፡ እንደው ፡ ቀጠሮ ፡ የለው

ለሕይወትህ ፡ ሰላም ፡ አግኝ ፡ እረፍትን
ና ፡ ብሎ ፡ ሲጠራ ፡ ዛሬ ፡ ነገ ፡ አትበል ፡ ስጠው ፡ ልብህን

አዝ፦ ኧረ ፡ ተው ፡ ወንድሜ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበል
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተል
ኧረ ፡ ተይ ፡ እህቴ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበይ
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተይ

ሀብት ፡ ቢሞላ ፡ ቢትረፈረፍ
ለነፍስ ፡ አንድም ፡ ጠብታ ፡ የለው
አንተነትህን ፡ የሚያረካ
ካለ ፡ ኢየሱስ ፡ ሁሉም ፡ ዘበት ፡ ነው

እረኝነቱ ፡ ሥር ፡ መጥተህ ፡ ተጠለል
ኢየሱስን ፡ ምረጠው ፡ ለነፍስ ፡ ለሥጋህ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ አትበል

አዝ፦ ኧረ ፡ ተው ፡ ወንድሜ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበል
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተል
ኧረ ፡ ተይ ፡ እህቴ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበይ
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተይ

ና ፡ ወደ ፡ እርሱ ፡ ጌታ ፡ ይፈታል
አንተነትህን ፡ ይለውጣል
በአዲስ ፡ ሕይወት ፡ በአዲስ ፡ ኑሮ
ልብህን ፡ ደስታ ፡ ይሞላል

ሰላምህ ፡ እንደ ፡ ወንዝ ፡ ሞልቶ ፡ ይፈሳል
ዋጋ ፡ አትከፍልበትም ፡ ወስን ፡ ወንድሜ ፡ ጌታ ፡ ይሻላል

አዝ፦ ኧረ ፡ ተው ፡ ወንድሜ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበል
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተል
ኧረ ፡ ተይ ፡ እህቴ ፡ ችላ ፡ ችላ ፡ አትበይ
ሕይወት ፡ ቀልድ ፡ አይደለም ፡ ይብቃ ፡ ዝላዩ ፡ ጌታን ፡ ተከተይ (፪x)