ሲታመኑት ፡ የሚታመን (Sitamenut Yemitamen) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 4.jpg


(4)

ቃልህ ፡ ቃሌና ፡ ግብሬ
(Qaleh Qaliena Gebrie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 6:07
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

ሲታመኑት ፡ የሚታመን
ቃሉን ፡ ደግሞ ፡ የማይበላ
የነገሩትን ፡ የማይረሳ
የለመኑትን ፡ የማይነሳ (፪x)

ኢየሱስ ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ
ኢየሱስ ፡ እርሱ ፡ ለእኔ ፡ አለኛ
ኢየሱስ ፡ አይወድቅ ፡ ቃሉ ፡ መሬት
ኢየሱስ ፡ ታማኝ ፡ ላመኑበት

ሲታመኑበት ፡ ታማኝ (፬x)
ሲታመኑበት ፡ ታማኝ (፬x)

ረዳት ፡ በሌለበት ፡ በዚያ ፡ ቦታ
ማን ፡ ተስፋ ፡ ይደረጋል ፡ ያለጌታ
ዓይኔን ፡ የጣልኩበት ፡ አንድ ፡ ዋሴ
ጥያቄዬ ፡ ገባው ፡ እየሱሴ

ኢየሱሴ (፪x) ፡ የጥያቄ ፡ ሁሉ ፡ መልሴ
ኢየሱሴ (፪x) ፡ ዋስ ፡ ጠበቃ ፡ ነው ፡ ለነፍሴ

ሲታመኑት ፡ የሚታመን
ቃሉን ፡ ደግሞ ፡ የማይበላ
የነገሩትን ፡ የማይረሳ
የለመኑትን ፡ የማይነሳ (፪x)

እየሱስ ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ
እየሱስ ፡ እሱ ፡ ለኔ ፡ አለኛ
እየሱስ ፡ አይወድቅ ፡ ቃሉ ፡ መሬት
እየሱስ ፡ ታማኝ ፡ ላመኑበት

ልቤን ፡ ወረሰና ፡ ወራሽ ፡ ሳይኖር
እንደኔማ ፡ ቢሆን ፡ ባልተገባኝ
ታሪኬን ፡ የሚያውቁ ፡ ጉድ ፡ ይበሉ
ሲያወጣኝ ፡ ሲያገባኝ ፡ እንደ ፡ ቃሉ
እንደ ፡ ቃሉ (፪x) ፡ ዝንፍ ፡ አይል ፡ አሰራሩ
እንደ ፡ ቃሉ ፡ ጌታ ፡ ቃሉ
አይሳሳት ፡ ስራው ፡ ምክሩ

ሲታመኑት ፡ የሚታመን
ቃሉን ፡ ደግሞ ፡ የማይበላ
የነገሩትን ፡ የማይረሳ
የለመኑትን ፡ የማይነሳ (፪x)

ኢየሱስ ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ
ኢየሱስ ፡ እርሱ ፡ ለእኔ ፡ አለኛ
ኢየሱስ ፡ አይወድቅ ፡ ቃሉ ፡ መሬት
ኢየሱስ ፡ ታማኝ ፡ ላመኑበት

በቃሉ ፡ የሰፈረው ፡ እንደዚህ ፡ ነው
የእኔ ፡ ነገር ፡ እኮ ፡ በእጁ ፡ ነው
አልሞትም ፡ በህይወት ፡ ልኑር ፡ እንጂ
ከበቂ ፡ በላይ ፡ ነው ፡ የአንተ ፡ እጅ

የአንተ ፡ እጅ (፪x) ፡ ከሰው ፡ በላይ ፡ የሚመች
የአንተ ፡ እጅ (፪x) ፡ መች ፡ ይጥላል ፡ ሚያነሳ ፡ እንጂ

ሲታመኑት ፡ የሚታመን
ቃሉን ፡ ደግሞ ፡ የማይበላ
የነገሩትን ፡ የማይረሳ
የለመኑትን ፡ የማይነሳ (፪x)

ኢየሱስ ፡ ሁልጊዜ ፡ እውነተኛ
ኢየሱስ ፡ እርሱ ፡ ለእኔ ፡ አለኛ
ኢየሱስ ፡ አይወድቅ ፡ ቃሉ ፡ መሬት
ኢየሱስ ፡ ታማኝ ፡ ላመኑበት