ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (Gieta Esu Becha New) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Lyrics.jpg


(1)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው
(Gieta Esu Becha New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:28
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

በላይ ፡ በላይ ፡ በላይ ፡ በሰማይ
በታች ፡ በታች ፡ ሆነህ ፡ በምድር ላይ (፪x)
 
አዝ፦ ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
አምላክ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው

ዛሬስ ፡ የታሉ ፡ ታላቅ ፡ ነን ፡ ያሉ
ዓመታት ፡ ሲያልፉ ፡ አብረው ፡ አለፉ
የሁሉ ፡ ገዢ ፡ የሁሉ ፡ የበላይ
የእኛ ፡ አምላክ ፡ ግን ፡ አለ ፡ በሰማይ (፭x)
 
አዝ፦ ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
አምላክ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
 
አላየሁኝም ፡ የሚመለክ ፡ እንደ ፡ እርሱ
አላየሁኝም ፡ የሚወደድ ፡ እንደ ፡ እርሱ
አልሰማሁኝም ፡ የሚመለክ ፡ እንደ ፡ እርሱ
አልሰማሁኝም ፡ የሚወደድ ፡ እንደ ፡ እርሱ
 
የምትወዱት ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ ተነሱ
የሚገባውን ፡ ክብር ፡ እንስጥ ፡ ለእርሱ (፪x)
 
በላይ ፡ በላይ ፡ በላይ ፡ በሰማይ
በታች ፡ በታች ፡ ሆነህ ፡ በምድር ላይ (፪x)

አዝ፦ ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
አምላክ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
 
የአህዛብ ፡ አማልክት ፡ የሚያመልኳቸው
የማይሰሙና ፡ ማያዩ ፡ ናቸው
ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ የሚመልሰው
የምናመልከው ፡ እግዚአብሔር ፡ ብቻ ፡ ነው (፬x)

አዝ፦ ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
አምላክ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ፍጥረት ፡ ወዶ ፡ ሚያመልከው
 
ያለውና ፡ የነበረው ፡ የሚመጣው
ሁሌ ፡ ሁሉን ፡ የሚገዛ ፡ ጌታ ፡ አምላክ ፡ ነው
አልፋ ፡ እና ፡ ኦሜጋ ፡ እኔ ፡ ነኝ ፡ ብሏል
ወዶ ፡ ፈቅዶ ፡ ፍጥረትም ፡ ያመልከዋል (፪x)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ
አምላክ ፡ እርሱ ፡ ብቻ
ገዢ ፡ እርሱ ፡ ብቻ
ንጉሥ ፡ እርሱ ፡ ብቻ (፪x)