አመሰግናለሁ (Amesegenalehu) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Lyrics.jpg


(1)

ጌታ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው
(Gieta Esu Becha New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

አዝ: አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

ፍቅሩ ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
ሥራው ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
 
አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)
 
ዘወትር ፡ ማለዳ ፡ ቀንና ፡ ሌሊቱ
እያልኩኝ ፡ አልፋለሁ ፡ አቤት ፡ ምህረቱ
ከመቅደሱ ፡ ሆኖ ፡ እርሱም ፡ ይሰማኛል
እኔስ ፡ ምሥጋናዬ ፡ በእርሱ ፡ ዘንድ ፡ ተወዷል
 
አዝ: ፍቅሩ ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
ሥራው ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
 
አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)
 
ቃላቶች ፡ ሳይወጡ ፡ የሚጐተጉቱ
አመስግነኝ ፡ ብሎ ፡ ጌታስ ፡ በአንደበቱ
ስራ ፡ እና ፡ ፍቅሩ ፡ መች ፡ ያስቀምጠኛል
ልቤስ ፡ በፈቃዱ ፡ ላመስግነው ፡ ብሏል
 
አዝ: ፍቅሩ ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
ሥራው ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው

አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

ልቤ ፡ አሰበ ፡ ፍቅሩን
እጅግ ፡ መወደዱን
ተነሳ ፡ ለአምልኮ
ጌታውን ፡ ፈልጐ (፪x)

ነፍሴ ፡ ታዳጊዋን ፡ ታመሰግናለች
ከአዳኞች ፡ ወጥመድ ፡ ድኛለው ፡ ትላለች
በፀናችው ፡ ክንዱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ታድጐ
የራሱ ፡ አድርጐኛል ፡ ምሥጋናን ፡ ፈልጐ
 
አዝ: ፍቅሩ ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
ሥራው ፡ ልቤን ፡ ተናገረው
እንዲያመልከው ፡ አነሳሳው
 
አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)
 
ልቤ ፡ አሰበ ፡ ፍቅሩን
እጅግ ፡ መወደዱን
ተነሳ ፡ ለአምልኮ
ጌታውን ፡ ፈልጐ (፪x)
 
አመሰግናለሁ ፡ አመሰግናለሁኝ ፡ አመሰግናለሁ