ይላል ፡ ገና (Yilal Gena) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 6:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

አምላኬ ፡ እድሌ ፡ ፈንታዬ
ያለመለምከው ፡ ተስፋዬን
መሞት ፡ ሲገባኝ ፡ ኩነኔ
እኔስ ፡ ገረመኝ ፡ መዳኔ (፪x)

ገረመኝ ፡ መዳኔ ፡ መዳኔ ፡ ገረመኝ ፡ መዳኔ (፪x)

ውለታ ፡ ያለበት ፡ መች ፡ ውስጡ ፡ ዝም ፡ ይላል
እየደጋገመ ፡ ምሥጋና ፡ ያሰማል
ፍቅሩን ፡ የቀመሰ ፡ መች ፡ ውስጡ ፡ ዝም ፡ ይላል
እየደጋገመ ፡ ምሥጋና ፡ ያሰማል

ያደረግልኝን ፡ ጌታ ፡ ይሆነልኝን
አስቤው ፡ ያን ፡ ዘመን ፡ በርሱ ፡ ያለፍኩትን

ክበር ፡ ልበለው ፡ እየደጋገምኩኝ
ንገሥ ፡ ልበለው ፡ እየደጋገምኩኝ
ክበር ፡ ልበለው ፡ አከብረዋለሁኝ
ንገሥ ፡ ልበለው ፡ አነግሰዋለሁኝ

ቅጥቅጥ ፡ ሸንበቆ ፡ አትሰብርም
የወደቀ ፡ አይተህ ፡ አታልፍም
አልቀረሁ ፡ ምስኪን ፡ ተብዬ
ባንተ ፡ ሰው ፡ ሆንኩኝ ፡ ጌታዬ (፪x)

ሰው ፡ ሆንኩኝ ፡ ጌታዬ (፫x)

ቃሉን ፡ ያሰበ ፡ መች ፡ ውስጡ ፡ ዝም ፡ ይላል
እየደጋገመ ፡ ምሥጋና ፡ ያሰማል
ከሞት ፡ ያመለጠ ፡ መች ፡ ውስጡ ፡ ዝም ፡ ይላል
እየደጋገመ ፡ ምሥጋና ፡ ያሰማል

ያደረግልኝን ፡ ጌታ ፡ ይሆነልኝን
አስቤው ፡ ያን ፡ ዘመን ፡ በርሱ ፡ ያለፍኩትን

ክበር ፡ ልበለው ፡ እየደጋገምኩኝ
ንገሥ ፡ ልበለው ፡ እየደጋተምኩኝ
ክበር ፡ ልበለው ፡ አከብረዋለሁኝ
ንገሥ ፡ ልበለው ፡ አነግሰዋለሁኝ

ቤቴ ፡ በክብሩ ፡ ተሞላና
እኔም ፡ ወግ ፡ አየሁ ፡ እንደገና (፪x)

ምሥጋና ፡ ምሥጋና ፡ ዝማሬ ፡ ዝማሬ
ሳልሰለች ፡ በደስታ ፡ ልዘምር ፡ ለጌታ

ከሆንኩለት ፡ በላይ ፡ ምነው ፡ በሆንኩለት (፫x)
ሕይወቴ ፡ ያማረው ፡ እርሱን ፡ ያገኘሁ ፡ እለት (፫x)
አንደበቴን ፡ ልክፈት ፡ በብዙ ፡ ምሥጋና (፫x)
በቅቶኝ ፡ አልቀመጥ ፡ ውስጤ ፡ ይላል ፡ ገና (፫x)

ውስጤ ፡ ይላል ፡ ገና ፡ ውስጤ ፡ ይላል ፡ ገና
ይላል ፡ ገና ፡ ውስጤ ፡ ይላል ፡ ገና (፪x)

ይላል ፡ ገና ፡ ምሥጋና
ይላል ፡ ገና ፡ ገናና
ይላል ፡ ገና ፡ አምልኮ
ይላል ፡ ገና ፡ ዝማሬ (፬x)