የደስታ ፡ መንፈስ (Yedesta Menfes) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

እኔስ ፡ በአምላኬ ፡ በጌቶች ፡ ጌታ
ይህ ፡ ነው ፡ አይባልም ፡ ያለኝ ፡ ደስታ
ደመና ፡ ሳይኖር ፡ በአካባቢዬ
ግራ ፡ ተጋብቷል ፡ ጠላት ፡ በደስታዬ (፫x)

አዝ፦ የደስታ ፡ መንፈስ ፡ በላዬ ፡ ወርዶ
ሃዘን ፡ ምሬቴን ፡ ከውስጤ ፡ ወስዶ
አመልከዋለሁ ፡ ከጠዋት ፡ ማታ
ኢየሱስ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ደስታ ፡ (ጌታ) (፬x)

የደስታዬ ፡ ምንጭ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆኖ
ሃዘኔ ፡ ጠፋ ፡ እንደጉም ፡ በንኖ
አላማርርም ፡ አላንጐራጉር
ደስተኛ ፡ ነኝ ፡ ሁሌ ፡ በእግዚአብሔር (፫x)

አዝ፦ የደስታ ፡ መንፈስ ፡ በላዬ ፡ ወርዶ
ሃዘን ፡ ምሬቴን ፡ ከውስጤ ፡ ወስዶ
አመልከዋለሁ ፡ ከጠዋት ፡ ማታ
ኢየሱስ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ደስታ ፡ (ጌታ) (፬x)

ማን ፡ ደስ ፡ ሊለው ፡ እኔ ፡ ልከፋ
በትንሽ ፡ ትልቁ ፡ ደስታዬ ፡ አይጠፋ
ለጠላት ፡ ወሬ ፡ ጆሮም ፡ አልሰጠው
ደስታዬ ፡ ፍጹም ፡ መቼም ፡ ማይወሰድ ፡ ነው (፫x)

አዝ፦ የደስታ ፡ መንፈስ ፡ በላዬ ፡ ወርዶ
ሃዘን ፡ ምሬቴን ፡ ከውስጤ ፡ ወስዶ
አመልከዋለሁ ፡ ከጠዋት ፡ ማታ
ኢየሱስ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ደስታ ፡ (ጌታ) (፬x)