በቃሉ ፡ የሚገኝ (Beqalu Yemigegn) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:23
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

ተስፋ ፡ ርቆ ፡ ሲዞር ፡ የሚደግፍ ፡ ጠፍቶ
ዘንበል ፡ የሚል ፡ ማነው ፡ እንደጌታ ፡ ራርቶ
ጊዜ ፡ ወቅቱን ፡ አይተው ፡ ሰዎች ፡ ሲቀየሩ
ጌታ ፡ ግን ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ ወረት ፡ የለው ፡ ፍቅሩ (፪x)

መሽቶ ፡ እስኪነጋ ፡ እስኪነጋ ፡ እስኪነጋ
ያለውን ፡ ሊፈጽም ፡ የሚተጋ ፡ የሚተጋ
አላየሁኝም ፡ በቃሉ ፡ የሚገኝ ፡ የሚገኝ
አምላኬ ፡ ብቻ ፡ ብቻውን ፡ ታማኝ (፪x)

ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ ፡ ጌታ
ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ (፪x)

ጌታዬ ፡ በአንተ ፡ ምኞቴ ፡ የልቤ ፡ ደረሰ
አንተን ፡ መታመኔ ፡ እኔ ፡ መች ፡ ከንቱ ፡ ነበረ (፪x)

እሰዪ ፡ የልቤ ፡ ደረሰ
ምርኮዬ ፡ በእርሱ ፡ ተመለሰ
ተሞላ ፡ ልቤ ፡ በደስታ
ልዘርም ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ ጌታ (፪x)

ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ ፡ ጌታ
ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ (፪x)

እንግዲህ ፡ ምን ፡ ልበል ፡ ጨለማዬ ፡ በራ
ከሸለቆ ፡ ወጣሁ ፡ ቆምኩኝ ፡ በተራራ (፪x)

ጌታዬ ፡ ባንተ ፡ ምኞቴ ፡ ያሰብኩት ፡ ተሳካ
አንተን ፡ መታመኔ ፡ እኔ ፡ ልክ ፡ ነበር ፡ ለካ (፪x)

ልክ ፡ ነው ፡ ጌታዬ ፡ ልክ ፡ ነው
እንዳለው ፡ ነው ፡ ለኔ ፡ ያደረገው
ሁኔታ ፡ ቃሉን ፡ አለወጠው
በእውነትም ፡ ጌታዬ ፡ ታማኝ ፡ ነው (፪x)

መሽቶ ፡ እስኪነጋ ፡ እስኪነጋ ፡ እስኪነጋ
ያለውን ፡ ሊፈጽም ፡ የሚተጋ ፡ የሚተጋ
አላየሁኝም ፡ በቃሉ ፡ የሚገኝ ፡ የሚገኝ
አምላኬ ፡ ብቻ ፡ ብቻውን ፡ ታማኝ

ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ ፡ ጌታ
ታማኝ ፡ ነዉ ፡ ታማኝ (፪x)

በሀሩሩ ፡ ጥላ ፡ ብርሃን ፡ በጨለማ
ምስኪን ፡ የምታግዝ ፡ ፀሎት ፡ የምትሰማ
በሀሩሩ ፡ ጥላ ፡ ብርሃን ፡ በጨለማ
እኔን ፡ የምታግዝ ፡ ፀሎት ፡ የምትሰማ