From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
የሰላም ፡ መፍለቂያ ፡ መንጭ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሰ ፡ አንተ ፡ እውነተኛ
ዓለም ፡ ለቀጣው ፡ ሰው ፡ ለተጐዳ ፡ መጽናኛ
የጠፋን ፡ ፈላጊ ፡ የኃጢአተኛ ፡ ወዳጅ
ለበዛው ፡ በደሉ ፡ ጠበቃ ፡ ነህ ፡ አማልላጅ
ስንቱ ፡ እረፍት ፡ አጥቶ ፡ ኖረ
መስሎት ፡ ብዙ ፡ ሞከረ
ለፋ ፡ ወጣ ፡ ገባ ፡ ፈልጐ ፡ አላገኘም
ምህረትህ ፡ ቀደመ ፡ ከንቱ ፡ ሆኖ ፡ አልቀረም
የሰላም ፡ መፍለቂያ ፡ መንጭ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሰ ፡ አንተ ፡ እውነተኛ
ዓለም ፡ ለቀጣው ፡ ሰው ፡ ለተጐዳ ፡ መጽናኛ
የጠፋን ፡ ፈላጊ ፡ የኃጢአተኛ ፡ ወዳጅ
ለበዛው ፡ በደሉ ፡ ጠበቃ ፡ ነህ ፡ አማልላጅ
እምቢ ፡ አሻፈረኝ ፡ ብሎ
ሄደ ፡ ቤትህን ፡ ጥሎ
በፍቅር ፡ አባብለህ ፡ መለስከው ፡ ያንን ፡ ሰው
አንተን ፡ መሳይ ፡ አባት ፡ ከየት ፡ ነው ፡ ሚገኘው
የሰላም ፡ መፍለቂያ ፡ መንጭ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሰ ፡ አንተ ፡ እውነተኛ
ዓለም ፡ ለቀጣው ፡ ሰው ፡ ለተጐዳ ፡ መጽናኛ
የጠፋን ፡ ፈላጊ ፡ የኃጢአተኛ ፡ ወዳጅ
ለበዛው ፡ በደሉ ፡ ጠበቃ ፡ ነህ ፡ አማልላጅ
ነፍሱን ፡ ለጠሉት ፡ ሁሉ ፡ ሲል
ሰጠ ፡ ተቆጠረ ፡ እንደ ፡ ቂል
የሰው ፡ ልጆች ፡ ክፋት ፡ እንዲህ ፡ እየጨመረ
ምትክ ፡ ሆኖ ፡ ባይሞት ፡ ምን ፡ ይኮን ፡ ነበረ?
የሰላም ፡ መፍለቂያ ፡ መንጭ ፡ ነህ ፡ ኢየሱሰ ፡ አንተ ፡ እውነተኛ
ዓለም ፡ ለቀጣው ፡ ሰው ፡ ለተጐዳ ፡ መጽናኛ
የጠፋን ፡ ፈላጊ ፡ የኃጢአተኛ ፡ ወዳጅ
ለበዛው ፡ በደሉ ፡ ጠበቃ ፡ ነህ ፡ አማልላጅ
|