ደባል ፡ አልፈልግም (Debal Alfelegem) - ካሌብ ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ካሌብ ፡ ተስፋዬ
(Caleb Tesfaye)

Lyrics.jpg


(5)

ሞትን ፡ የረታ ፡ ጌታ
(Moten Yereta Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:34
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የካሌብ ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Caleb Tesfaye)

አዝ፦ ደባል ፡ አልፈልግም ፡ ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ አጠጥቶ ፡ አርክቶኛል
የእረፍቴ ፡ ባለቤት ፡ የዘለዓለም ፡ ደስታ
አገዘ ፡ ድካሜን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ (፪x)

ቀንበር ፡ የከበደው ፡ ብዙ ፡ ሸክም ፡ የተጫነው
የሚያሳርፍ ፡ አጥቶ ፡ የባዘነን ፡ እንደኔ ፡ ማነው
የችግር ፡ ቀን ፡ ወዳጅ ፡ ባልንጀራ ፡ ከጐኔ ፡ ጠፍቶ
ደርሶ ፡ የታደገኝ ፡ ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ እኔ ፡ ድረስ ፡ መጥቶ

አዝ፦ ደባል ፡ አልፈልግም ፡ ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ አጠጥቶ ፡ አርክቶኛል
የእረፍቴ ፡ ባለቤት ፡ የዘለዓለም ፡ ደስታ
አገዘ ፡ ድካሜን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ (፪x)

ሁሉን ፡ አሳልፎ ፡ ለቁም ፡ ነገር ፡ እኔን ፡ ሲያበቃ
ክብሩን ፡ ለሌላ ፡ አልሰጥ ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ እየረዳኝ
ውርደቴን ፡ ለወጠ ፡ ተራ ፡ ደርሶኝ ፡ አሳረፈኝ
ሜዳ ፡ ተራራውን ፡ ሰርጓጐቱን ፡ አሳለፈኝ

አዝ፦ ደባል ፡ አልፈልግም ፡ ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ አጠጥቶ ፡ አርክቶኛል
የእረፍቴ ፡ ባለቤት ፡ የዘለዓለም ፡ ደስታ
አገዘ ፡ ድካሜን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ (፪x)

ወዲህ ፡ ወዲያ ፡ አልል ፡ አልቅበዘበዝ ፡ ከእንግዲህማ
ጩኸቴ ፡ በአምላኬ ፡ ልመናዬ ፡ ከተሰማ
መድኃኒቴ ፡ ሆነኝ ፡ ፈውሶኛል ፡ ያለ ፡ ጠባሳ
ቀረ ፡ መጨነቄ ፡ ሄዶልኛል ፡ ያ ፡ ሁሉ ፡ አበሳ

አዝ፦ ደባል ፡ አልፈልግም ፡ ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ አጠጥቶ ፡ አርክቶኛል
የእረፍቴ ፡ ባለቤት ፡ የዘለዓለም ፡ ደስታ
አገዘ ፡ ድካሜን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ (፪x)

በሌላ ፡ ሲመካ ፡ ባለው ፡ ሃብቱ ፡ ሲንጠራራ
ልቡ ፡ አውቆ ፡ በትዕቢት ፡ በሚጠፋ ፡ በራሱ ፡ ሲኩራራ
የሚመካ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ይመካ ፡ በኃያሉ
ተስፋ ፡ ሰጥቶ ፡ አይክድም ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እርሱ ፡ በቃሉ

አዝ፦ ደባል ፡ አልፈልግም ፡ (ደባል ፡ አልፈልግም)
ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል ፡ (ኢየሱስ ፡ ይበቃኛል)
የሕይወት ፡ ምንጭ ፡ ውኃ ፡ አጠጥቶ ፡ አርክቶኛል
የእረፍቴ ፡ ባለቤት ፡ (የእረፍቴ ፡ ባለቤት)
የዘለዓለም ፡ ደስታ ፡ (የዘለዓለም ፡ ደስታ)
አገዘ ፡ ድካሜን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የእኔ ፡ መከታ (፪x)