ያለፍነውን (Yalefnewen) - ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ
(Bezu Mulugeta)

Lyrics.jpg


(2)

ኢየሱስ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ አልን! እንደገና
(Eyesus Leyu New Alen Endegena)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፩ (1998)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Bezu Mulugeta)

ያለፍነውን ፡ ያሳለፈን ፡ አረማነው
ዮርዳኖስን ፡ የከፈለው ፡ አረ ፡ ማነው
ማነው (፪x) ፡ አረማነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ብርቱ ፡ ሃያል
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ በሰልፍ ፡ ኃያል (፪x)

፩) ኃጢአታችን ፡ እጅግ ፡ በዝቶ
ነፍሳችንን ፡ አስጨንቆ
መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በኛ ፡ አዝኖ
ሀይወታችን ፡ ተበላሽቶ

የተቤዥን ፡ በምህረቱ ፡ ያስታረቀን ፡ ከአባቱ
የዘላለም ፡ ጠባቂያችን ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ እረኛችን
እንደ ፡ እግዚአብሄር ፡ ለዘላለም
የሚችለን ፡ ማንም ፡ የለም

፪) በባዕድ ፡ ምድር ፡ ስንጨቆን
ስንገዛ ፡ በፈርኦን
መከራችን ፡ የተሰማው
ሃዘናችን ፡ ያሳዘነው

እስራትን ፡ የሰበረ ፡ ቀንበሩንም ፡ የሰበረ
ባለድሎች ፡ ያደረገን ፡ መልካም ፡ ነገር ፡ ያጠገበን
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ለዘላለም
የሚረዳን ፡ ማንም ፡ የለም

፫) የእኛን ፡ መውደቅ ፡ የተመኙ
ጉድጓዳችንን ፡ የቆፈሩ
በእጃቸው ፡ ተንኮል ፡ ይዘው
ወጥመዶችን ፡ ለእኛ ፡ አጥምደው

ዛሬ ፡ ነገ ፡ ጠፋ ፡ ያለ ፡ የኛን ፡ ረዳት ፡ ያላወቁ
እጃቸውን ፡ በአፋቸው ፡ አድርገዋል ፡ በስራቸው
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ለዘላለም
የሚያጸናን ፡ ማንም ፡ የለም