እግዚአብሔር ፡ በከፍታው (Egziabhier Bekefetaw) - ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ
(Bezu Mulugeta)

Lyrics.jpg


(2)

ኢየሱስ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ አልን! እንደገና
(Eyesus Leyu New Alen Endegena)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፩ (1998)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ እና ፡ ወንጌላዊ ፡ ተድላ ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Bezu Mulugeta)

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው

፩) ፈርኦን ፡ ሊገዛ ፡ እስራኤልን
ልቡን ፡ አደንድኖ ፡ ከፍ ፡ ቢልም
ሕዝቡን ፡ ለመታደግ ፡ የቆረጠው
የሰራዊት ፡ ጌታ ፡ አሸነፈው

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው

፪) ዳንኤል ፡ ቢጣልም ፡ በጉድጓዱ
አንበሳ ፡ እንዲበላው ፡ ቢታዘዝ
የኃያላን ፡ ሀያል ፡ ኢየሱስ
አዳነ ፡ ካንበሳው ፡ ባሪያውን

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው

፫) መከራ ፡ ቢከበን ፡ ዙሪያችን
ተቆረጠ ፡ ስንል ፡ ተስፋችን
በከፍታዎች ፡ ላይ ፡ ከፍ ፡ የሚል
ልዑል ፡ አምላካችን ፡ ባለድል

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው

፬) አይሆንም ፡ ተብሎ ፡ ተቆርጦ
ተስፋዬ ፡ በሙሉ ፡ ተሟጦ
እግዚአብሔር ፡ ቃሉን ፡ አሰበ
ነገር ፡ በጊዜው ፡ ጨኮለ

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው

፭) አፍ ፡ ባለው ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ ከፍ ፡ ብሎ
በከፍታዎች ፡ ላይ ፡ ድንቅ ፡ ሆኖ
የኖረ ፡ ሳይረታ ፡ ዘላለም
እግዚአብሔርን ፡ የሚመስል ፡ የለም

አዝእግዚአብሔር ፡ በከፍታው ፡ ድንቅ ፡ ነው (፪x)
እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው