ወዴት ፡ አለህ (Wediet Aleh) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 3.jpg


(3)

ዕድሜዬ ፡ በቤትህ ፡ ይለቅ
(Edmieyie Bebieteh Yileq)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

ልቤ ፡ ዋተተ ፡ ዋተተ
መንፈሴም ፡ ታወከብኝ
ልጄ ፡ አንተን ፡ አጥቼ ፡ ከጉያዬ
እንዴት ፡ ልረፍ ፡ በምን ፡ anjet chye

እህ ፡ እህህህህ
እህህ ፡ ሆነብኝ ፡ ጠዋት ፡ ማታ
ወንድሞችህ ፡ ቢኖሩም ፡ በቤት
አይተኩትም ፡ ለአንተ ፡ ያለኝን ፡ ቦታ

አዝ፦ ወዴት ፡ አለህ
ድምጼን ፡ ሰምተህ ፡ አለሁ ፡ በለኛ
ፈጠን ፡ ብለህ ፡ ወደ ፡ እቅፌ ፡ ግባ (፪x)

ደጅ/በር ፡ አፍ ፡ ላይ ፡ ቆሞ ፡ ያንኳኳል ፡ ወዳጅ
ይጣራል ፡ ወዳጅ (፪x)
ድምጹን ፡ ሲያሰማ ፡ አስገባው ፡ ከፍተህ
አይጥና ፡ ደጅ ፣ አይጥና ፡ ደጅ (፪x)

እናት ፡ ትረሳ ፡ ይሆናል ፡ አምጣ ፡ የወለደችውን
እኔማ ፡ እንዴት ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ እንዴት
አንተን ፡ ጥሎ ፡ መኖር ፡ በሞቀ ፡ ቤት
ልጄን ፡ ካልያዝኩት ፡ አልረካ
ክርትት ፡ አለ ፡ ዓይኔ ፡ አንተን ፡ ፍለጋ
ወድሃለሁ ፡ ልጄ ፡ ናና ፡ ናና
ሙሉ ፡ እንዲሆን ፡ የቤቴ ፡ ምሥጋና

አዝ፦ ወዴት ፡ አለህ
ድምጼን ፡ ሰምተህ ፡ አለሁ ፡ በለኛ
ፈጠን ፡ ብለህ ፡ ወደ ፡ እቅፌ ፡ ግባ (፪x)

ደጅ/በር ፡ አፍ ፡ ላይ ፡ ቆሞ ፡ ያንኳኳል ፡ ወዳጅ
ይጣራል ፡ ወዳጅ (፪x)
ድምጹን ፡ ሲያሰማ ፡ አስገባው ፡ ከፍተህ
አይጥና ፡ ደጅ ፣ አይጥና ፡ ደጅ (፪x)

አባ ፡ አባባ ፡ ስትለኝ
እስቲ ፡ ልስማህ ፡ ያ ፡ ድምጽህ ፡ ናፈቀኝ
ሸክምህን ፡ አውርድ ፡ ከጫንቃህ
ላሳርፍህ ፡ አለሁ ፡ አባትህ

የሚያሳየው ፡ ጐልጐታ
ዛሬም ፡ ያው ፡ ነው ፡ ፍቅሬ ፡ መች ፡ ተገታ
በላ ፡ እንሂድ ፡ ወደ ፡ ቤታችን
እኔም ፡ ልረፍ ፡ አግኝቼ ፡ አንተን

አዝ፦ ወዴት ፡ አለህ
ድምጼን ፡ ሰምተህ ፡ አለሁ ፡ በለኛ
ፈጠን ፡ ብለህ ፡ ወደ ፡ እቅፌ ፡ ግባ

(ወዴት ፡ አለህ) ፡ ወዴት ፡ አለህ
(ድምጼን ፡ ሰምተህ) ፡ ድምጼን ፡ ሰምተህ
አለሁ ፡ በለኛ ፡ (አለሁ ፡ በለኛ)
ፈጠን ፡ ብለህ ፡ ወደ ፡ እቅፌ ፡ ግባ (፪x)