ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር (Leafeh Tebaqi Anur) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 3.jpg


(3)

ዕድሜዬ ፡ በቤትህ ፡ ይለቅ
(Edmieyie Bebieteh Yileq)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:56
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

አዝ፦ አንደበቱን ፡ የሚገታ ፡ ሰውነቱን ፡ ይገዛልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር

አንደበቱን ፡ የሚጠብቅ ፡ ነፍሱን ፡ ይጠብቃታልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር

አመጸኛ ፡ አለ ፡ ሙሉ ፡ ሥጋውን ፡ ያሳድፋል
ትንሽ ፡ እሳት ፡ እንዴት ፡ ያለ ፡ ትልቅ ፡ ጫካ ፡ ያጋያል
ከአንድ ፡ ምንጭ ፡ መራርና ፡ ጣፋጭ ፡ እንዳይቀዳ
ከአንደበትህ ፡ አንዴ ፡ መርገም ፡ አንዴ ፡ ባርኮት ፡ አይውጣ

ፈዋሽ ፡ ምላስ ፡ የሕይወት ፡ ዛፍ ፡ ናት
መልካም ፡ ፍሬ ፡ ሚለቀምባት
የጠቢብ ፡ ቃል ፡ እንደምንጭ ፡ ነው
የተፍገመገመውን ፡ የሚያቀናው (፪x)

አዝ፦ አንደበቱን ፡ የሚገታ ፡ ሰውነቱን ፡ ይገዛልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር

አንደበቱን ፡ የሚጠብቅ ፡ ነፍሱን ፡ ይጠብቃታልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር

መልካም ፡ ዘመን ፡ ማየት ፡ ካሻህ ፡ አፍህን ፡ ከክፉ ፡ ከልክል
በቃል ፡ ብዛት ፡ ኃጢአት ፡ ሳይኖር ፡ አይቀርምና ፡ አስተውል
ልብ ፡ የሞላውን ፡ ያንኑ ፡ አፍ ፡ ይናገራልና
ጆሮህን ፡ ለትምህርት ፡ አቅና ፡ ጥበብ ፡ ልብህን ፡ ይሙላ

ፈዋሽ ፡ ምላስ ፡ የሕይወት ፡ ዛፍ ፡ ናት
መልካም ፡ ፍሬ ፡ ሚለቀምባት
የጠቢብ ፡ ቃል ፡ እንደምንጭ ፡ ነው
የተፍገመገመውን ፡ የሚያቀናው (፪x)

አዝ፦ አንደበቱን ፡ የሚገታ ፡ ሰውነቱን ፡ ይገዛልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር

አንደበቱን ፡ የሚጠብቅ ፡ ነፍሱን ፡ ይጠብቃታልና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር
የሕይወት ፡ ቃል ፡ መውጫ ፡ በር ፡ ናትና
ዘሯም ፡ ሲያፈራ ፡ እጥፍ ፡ ነውና
ለአፍህ ፡ ጠባቂ ፡ አኑር