አልጠግብ ፡ ባይነት (Altegeb Bayenet) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 3.jpg


(3)

ዕድሜዬ ፡ በቤትህ ፡ ይለቅ
(Edmieyie Bebieteh Yileq)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

እኔ
እኔ ፡ እኔ
ዛሬም ፡ እኔ ፡ ነገም ፡ እኔ
ወሬ ፡ እኔ ፡ ስጠኝ ፡ ለእኔ
ልመናዬም ፡ እኔ (፬x)
እዎይ ፡ አልጠግብ ፡ ወይነቴ
አዎይ ፡ አልረካም ፡ ወይነቴ

አዝ፦ አንተ ፡ የሞትክልኝ ፡ ጐልጐታ ፡ አናት ፡ ላይ
ከሠማዩ ፡ ክብር ፡ እንድሆን ፡ ተካፋይ
እኔ ፡ እዚህ ፡ ስዳክር ፡ ልጨብጥ ፡ ምድርን
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መምሰል
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መውደድ
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር

ሊበሉ ፡ የመጡ ፡ ለእንጀራቸው
ሊፈወሱ ፡ ብለው ፡ ለጤናቸው
አመስግነው ፡ ባርከው ፡ ሳይበቃቸው
ተከተሉ ፡ እያሉ ፡ ስቀለው ፡ ስቀለው

አዝ፦ አንተ ፡ የሞትክልኝ ፡ ጐልጐታ ፡ አናት ፡ ላይ
ከሠማዩ ፡ ክብር ፡ እንድሆን ፡ ተካፋይ
እኔ ፡ እዚህ ፡ ስዳክር ፡ ልጨብጥ ፡ ምድርን
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መምሰል
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መውደድ
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር

እኔ ፡ እኔ
ዛሬም ፡ እኔ ፡ ነገም ፡ እኔ
ወሬ ፡ እኔ ፡ ስጠኝ ፡ ለእኔ
ልመናዬም ፡ እኔ (፬x)
እዎይ ፡ አልጠግብ ፡ ወይነቴ
አዎይ ፡ አልረካም ፡ ወይነቴ

አዝ፦ አንተ ፡ የሞትክልኝ ፡ ጐልጐታ ፡ አናት ፡ ላይ
ከሠማዩ ፡ ክብር ፡ እንድሆን ፡ ተካፋይ
እኔ ፡ እዚህ ፡ ስዳክር ፡ ልጨብጥ ፡ ምድርን
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መምሰል
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መውደድ
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር

እንዲያገለግሉት ፡ ቢጠራቸው
ከባርነት ፡ ፈትቶ ፡ ቢለቃቸው
ሆዳቸው ፡ አምላካቸው ፡ ሆነባቸው
ሥጋ ፡ በልተው ፡ ሞቱ ፡ ሜዳ ፡ ቀረ ፡ ሬሳቸው

አዝ፦ አንተ ፡ የሞትክልኝ ፡ ጐልጐታ ፡ አናት ፡ ላይ
ከሠማዩ ፡ ክብር ፡ እንድሆን ፡ ተካፋይ
እኔ ፡ እዚህ ፡ ስዳክር ፡ ልጨብጥ ፡ ምድርን
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መምሰል
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር
እንዳልቀር ፡ አንተን ፡ መውደድ
እንዴት ፡ ነው ፡ ልማር

አንድ ፡ ነገር ፡ እለምንህ ፡ እንድትረዳኝ
እንጀራ ፡ ሰጥተኸኝ ፡ እንዳትሄድብኝ
አንድ ፡ ነገር ፡ እሻለሁኝ ፡ እንድትረዳኝ
እንጀራ ፡ አብልተኸኝ ፡ እንዳትሄድብኝ (፫x)