እመለሳለሁ (Emelesalehu) - አዜብ ፡ መለሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ መለሰ
(Azeb Melesse)

Azeb Melesse 1.jpeg


(1)

የነፍስ ፡ አባቴ
(Yenefs Abatie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ መለሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Melesse)

 
አዝ:- ብዙዎች ፡ እንደፈለጋቸው
አንተንም ፡ ሳይፈሩ ፡ የሚኖሩ ፡ ናቸው
ሲላቸው ፡ እንደምኞታቸው ፡ ቃልህን ፡ ይገልጻሉ
እራሳቸው ፡ ስተው ፡ ሌላውን ፡ ያስታሉ

አሉ ፡ ደግሞ ፡ ጥቂት ፡ አንተን ፡ የሚፈሩ
ምህረትህን ፡ ታምነው ፡ በጽድቅ ፡ የሚኖሩ
ታጋሽ ፡ ቸር ፡ ሩህሩህ ፡ ምህረትህ ፡ የበዛ
ለእነሱ ፡ ደግ ፡ ነህ ፡ ጨካኝ ፡ ከተቆጣ

እኔ ፡ ከእነዚህ ፡ ጋር ፡ ፈጥኜ ፡ እስማማለሁ
ላለፈው ፡ በደሌ ፡ ንስሃ ፡ እገባለሁ
ድንገት ፡ ሳትጥለኝ ፡ ዛሬ ፡ እመለሳለሁ

እመለሳለሁ ፡ ፍሬም ፡ ማያፈራ ፡ የደረቀ ፡ እንጨት
ማይጠቅም ፡ ዛፍ ፡ ተቆርጦ ፡ መጣል ፡ ነው ፡ በማይጠፋው ፡ እሳት
ልትመጣ ፡ ነው ፡ ክብርህን ፡ ልትገልጥ ፡ ቤትህን ፡ ልታጠራ
ኀጢአት ፡ ልትቀጥፍ ፡ ጅራፍህን ፡ ይዘህ ፡ ተነስተሃልና
አይሆንም ፡ ብሎ ፡ ማነው ፡ ባለስልጣን ፡ የሚከለክልህ
እንዴ ፡ ከያዝከኝ ፡ የትኛው ፡ ብርቱ ፡ ነው ፡ ከእጅህ ፡ የሚያስጥለኝ
እመለሳለሁ ፡ የኔ ፡ መጨረሻ ፡ የኔ ፡ እድል ፡ ፈንታዬ
እመለሳለሁ ፡ እንደ ፡ እንጨቱ ፡ እንዳይሆን ፡ መልሰኝ ፡ ጌታዬ
መልሰኝ ፡ ጌታዬ ፡ መልሰኝ

አዝ:- ብዙዎች ፡ እንደፈለጋቸው
አንተንም ፡ ሳይፈሩ ፡ የሚኖሩ ፡ ናቸው
ሲላቸው ፡ እንደምኞታቸው ፡ ቃልህን ፡ ይገልጻሉ/ይጠቅሳሉ
እራሳቸው ፡ ስተው ፡ ሌላውን ፡ ያስታሉ (፬x)