Azeb Hailu/Embi/Temesgen

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search


ጽድቅን እንዲያወራ ምላሴ

እንድትረካ እንድታርፍ ነፍሴ

የዋጀኸኝ አምላኬ መድህኔ

ከዚህች ዓለም አመጻ ኩነኔ


እንዳይረክስ በከንቱ ከንፈሬ

እንዳልጥለው ውድ እንቁውን ክብሬ

ዘመኔን በእጆችህ ያዝክና

አራመድከኝ በሕይወት ጐዳና


አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ

ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)



እንድረዳ ማዳንህን እንዳውቀው

ልቦናዬን ወዳንተ የመለስከው

እንዳያልፈኝ የሕይወቴ መና

ህሊናዬን ለቃልህ አቀናህ


በረከሰው ዓለም የቀደስከኝ

በጽድቅ መንገድ ላይ የመራኸኝ

ከብዙዎች እኔ ተለይቼ

ዘምራለሁ መቅደስህ ገብቼ


አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ

ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)


አልመኝም ከእንግዲህ ወደ ውጪ

ረክቻለሁ ጌታ አንተን መርጬ

የዓለምን ከንቱነት ኮተቷን

ንቄዋለሁ ከነማንነቷ


ወስኛለሁ ልኖር አስከብሬህ

ላፈራልህ ጣፋጭ መልካም ፍሬ

ደስ እንዲልህ ሁሌ በእኔ ጌታ

እገዛለሁ ፈቅጄ በደስታ


አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ

ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)