From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት ።
|
|
አዜብ ፡ ኃይሉ (Azeb Hailu)
|
|
፩ (1)
|
እምቢ (Embi)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
|
ቁጥር (Track):
|
፱ (9)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች (Albums by Azeb Hailu)
|
|
ጽድቅን ፡ እንዲያወራ ፡ ምላሴ
እንድትረካ ፡ እንድታርፍ ፡ ነፍሴ
የዋጀኸኝ ፡ አምላኬ ፡ መድህኔ
ከዚህች ፡ ዓለም ፡ አመጻ ፡ ኩነኔ
እንዳይረክስ ፡ በከንቱ ፡ ከንፈሬ
እንዳልጥለው ፡ ውድ ፡እንቁውን ፡ ክብሬ
ዘመኔን ፡ በእጆችህ ፡ ያዝክና
አራመድከኝ ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና
አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን
ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ ደግሜ
ከኃጢአት ፡ በሽታ ፡ ተፈውሼ ፡ ባንተ ፡ ታክሜ (፪x)
እንድረዳ ፡ ማዳንህን ፡ እንዳውቀው
ልቦናዬን ፡ ወዳንተ ፡ የመለስከው
እንዳያልፈኝ ፡ የሕይወቴ ፡ መና
ህሊናዬን ፡ ለቃልህ ፡ አቀናህ
በረከሰው ፡ ዓለም ፡ የቀደስከኝ
በጽድቅ ፡ መንገድ ፡ ላይ ፡ የመራኸኝ
ከብዙዎች ፡ እኔ ፡ ተለይቼ
ዘምራለሁ ፡ መቅደስህ ፡ ገብቼ
አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን
ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ ደግሜ
ከኃጢአት ፡ በሽታ ፡ ተፈውሼ ፡ ባንተ ፡ ታክሜ (፪x)
አልመኝም ፡ ከእንግዲህ ፡ ወደ ፡ ውጪ
ረክቻለሁ ፡ ጌታ ፡ አንተን ፡ መርጬ
የዓለምን ፡ ከንቱነት ፡ ኮተቷን
ንቄዋለሁ ፡ ከነማንነቷ
ወስኛለሁ ፡ ልኖር ፡ አስከብሬህ
ላፈራልህ ፡ ጣፋጭ ፡ መልካም ፡ ፍሬ
ደስ ፡ እንዲልህ ፡ ሁሌ ፡ በእኔ ፡ ጌታ
እገዛለሁ ፡ ፈቅጄ ፡ በደስታ
አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን
ተመስገን ፡ ልበልህ ፡ ደግሜ
ከኃጢአት ፡ በሽታ ፡ ተፈውሼ ፡ ባንተ ፡ ታክሜ (፪x)
|