From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
አዜብ ፡ ኃይሉ (Azeb Hailu)
|
|
፩ (1)
|
እምቢ (Embi)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
|
ቁጥር (Track):
|
፲ (10)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች (Albums by Azeb Hailu)
|
|
አላደርግም ፡ ለሌላ ፡ ስግደት ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ አባት (፪x)
አልችልም ፡ ለሌላ ፡ መንበርከክ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ አምላክ (፪x)
አላሰማም ፡ ለሌላ ፡ እልልታ ፡ ላንተ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ይህ ፡ ጌታ (፪x)
እኔ ፡ አልሰዋም ፡ ለሌላ ፡ አምልኮ ፡ ለሥምህ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ እኮ (፪x)
አዝ፦ ምላስ ፡ ሁሉ ፡ ያንተን ፡ ክብር ፡ ይናገረው ፡ ያውራ (፪x)
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ተንበርክኮ ፡ ይደነቅ ፡ በስራህ (፪x)
ባሕር ፡ ከፍለህ ፡ ሕዝብህን ፡ ማሻገርህን
የልጆችህን ፡ ጠላት ፡ በዚያ ፡ ማስጠምህን
በምድረ ፡ በዳው ፡ ላይ ፡ መናን ፡ ማውረድህን
ከደረቀው ፡ አለት ፡ ውሃ ፡ ማፍለቅህን
(ኦሆ) ፡ ታምራትህ ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይናገረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ታምራትህን ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይዘምረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ
አዝ፦ ምላስ ፡ ሁሉ ፡ ያንተን ፡ ክብር ፡ ይናገረው ፡ ያውራ (፪x)
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ተንበርክኮ ፡ ይደነቅ ፡ በስራህ (፪x)
የማይፈወሰውን ፡ ደዌ ፡ ማዳንህን
የሞተውን ፡ ከመቃብር ፡ ማንሳትህን
ሁለት ፡ ዓሣ ፡ ለአምስት ፡ ሺህ ፡ ማጥገብህን
በውሃም ፡ ላይ ፡ መሄድ ፡ መጓዝ ፡ መቻልህን
(ኦሆ) ፡ ታምራትህ ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይናገረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ታምራትህን ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይዘምረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ
አዝ፦ ምላስ ፡ ሁሉ ፡ ያንተን ፡ ክብር ፡ ይናገረው ፡ ያውራ (፪x)
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ተንበርክኮ ፡ ይደነቅ ፡ በስራህ (፪x)
ስለ ፡ ሰዎች ፡ ሃጥያት ፡ ራስህን ፡ መስጠትህን
በመስቀል ፡ ላይ ፡ ተቸንክረህ ፡ መሞትህን
ከሙታንም ፡ በኩር ፡ ሆነህ ፡ መውጣትህን
በአባትህ ፡ ቀኝ ፡ ኦ ፡ በክብር ፡ መሆንህን
(ኦሆ) ፡ ታምራትህ ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይናገረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ታምራትህን ፡ (ኦሆ) ፡ ድንቅህን ፡ ሁሉ
(ኦሆ) ፡ ይመስክረው ፡ (ኦሆ) ፡ ምላስ ፡ ሁሉ (፪x)
|