ቃልህ (Qaleh) - አይዳ ፡ አብርሃም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አይዳ ፡ አብርሃም
(Ayda Abraham)

Ayda Abraham 1.jpg


(1)

ስላንተ
(Selante)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2014)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 5:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአይዳ ፡ አብርሃም ፡ አልበሞች
(Albums by Ayda Abraham)

አቤቱ ፡ ቃልህ ፡ እውንት ፡ ነው
የተናገርከውም ፡ እውነት ፡ ነው
አቤቱ ፡ ቃልህ ፡ ሕይወት ፡ ነው
ከአንተ ፡ የሚወጣው ፡ ሕይወት ፡ ነው

ሰምቶ ፡ ላመነበት ፡ እውነት ፡ ነው
አምኖ ፡ ላረገውም ፡ ሕይወት ፡ ነው /2

ነብሴ ፡ አውቃለች ፡ እውነት ፡ መሆንህን
ነብሴ ፡ አውቃለች ፡ ሰላም ፡ መሆንህን
ያለ ፡ ቃልህ ፡ ሕይወት ፡ የለም ፡ ብላ
ታመልክሃለች ፡ ሁሉን ፡ ነገር ፡ ጥላ

አዎ ፡ ነብሴ ፡ ሚታየውን ፡ ትታ
አዎ ፡ ነብሴ ፡ ሚሰማውን ፡ ትታ
ነብሴ ፡ ነብሴ ፡ የውጭውን ፡ ትታ
ነብሴ ፡ ነብሴ ፡ ፡ ሁኔታውን ፡ ትታ

ያቆመኛል ፡ አለች ፡ ቃልህን ፡ ተጠግታ
ያቆመኛል ፡ አለች ፡ ቃልህን ፡ ተጠግታ

እውነት ፡ ነው ፡ እውነት ፡ ነው ፡ ትረዳታለህ
እውነት ፡ ነው ፡ እውነት ፡ ነው ፡ ታቆማታለህ
እውነት ፡ ነው ፡ እውነት ፡ ነው ፡ ታፀናታለህ
እውነት ፡ ነው ፡ እውነት ፡ ነው ፡ ፡ ትረዳታለህ

ከምንም ፡ ከማንም ፡ ትበልጥባታለህ
በሚረባት ፡ መንገድም ፡ ታስኬዳታለህ /2

በፊትህማ ፡ ምታገኘው ፡ ሰላም
በፊትህማ ፡ ምታገኘው ፡ ፡ ደስታ
በቃልህማ ፡ ምታፈኘው ፡ እረፍት
በቃልህማ ፡ ምታፈኘው ፡ አቅም

ማን ፡ ሊተካው ፡ ለእርሳ ፡ ማን ፡ ሊተካው ፡ ለእርሳ
እውነት ፡ ነው ፡ እግዚአብሔር ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ንጉሷ

አንተ ፡ ነህ ፡ ንጉሷ ፡ የጥያቄ ፡ መልሷ
አንተን ፡ ታይሃለች ፡ አንተን ፡ ታይሃለች
አንተን ፡ ፡ ትሠማለች ፡ አንተን ፡ ትሠማለች
ትደገፍሃለች ፡ ትደገፍሃለች ፡ ትደገፍሃለች ፡ ትደገፍሃለች