From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
አውታሩ ፡ ከበደ (Awtaru Kebede)
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
ተነስቷል (Tenestual)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
|
ቁጥር (Track):
|
፲ (10)
|
ርዝመት (Len.):
|
3:25
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአውታሩ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች (Albums by Awtaru Kebede)
|
|
በጓዳዬ ፡ ሆኜ ፡ ቅዱስ ፡ ነው ፡ ስለው
በአደባባይ ፡ ላይ ፡ ሥራዬን ፡ ሰራው
ልቤ ፡ ቅልጥ ፡ አለ ፡ በፍቅሩ ፡ ትኩሳት
ሰላም ፡ ነው ፡ የሞላው ፡ ብትገቡ ፡ በእኔ ፡ ቤት
አሃሃ ፡ ከምድር ፡ በታች ፡ ከዚያም ፡ በላይ
እኔ ፡ አላየሁም ፡ እርሱን ፡ መሳይ (፪x)
አብ ፡ ያከበረ ፡ ጌታ ፡ እርሱን ፡ ብቻ
ለውበቱማ ፡ የለውም ፡ አቻ (፪x)
ዝምታ ፡ ሆነ ፡ ፀጥታ
አካባቢው ፡ ላይ ፡ ምን ፡ መጣ
ምትሃት ፡ አይደለም ፡ ጌታ ፡ ነው
ማዕበል ፡ ወጀቡን ፡ ያቆመው (፪x)
ጌታ ፡ ነው (፪x) ፡ ከሁሉ ፡ በላይ
ከሁሉ ፡ በላይ
በሰማይ ፡ በምድር ፡ የለም ፡ የሚታይ
የለም ፡ የሚታይ
እስቲ ፡ ከእርሱ ፡ በላይ ፡ ማነው ፡ የበላይ
ማኅተሙን ፡ የፈታ ፡ ይታወቃል ፡ ዎይ
እስቲ ፡ ከእርሱ ፡ በላይ ፡ ማነው ፡ የበላይ
ሞትን ፡ ድል ፡ የነሳ ፡ ይታወቃል ፡ ዎይ
አሃሃ ፡ ከምድር ፡ በታች ፡ ከዚያም ፡ በላይ
እኔ ፡ አላየሁም ፡ እርሱን ፡ መሳይ (፪x)
አብ ፡ ያከበረ ፡ ጌታ ፡ እርሱን ፡ ብቻ
ለውበቱማ ፡ የለውም ፡ አቻ (፪x)
|