From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አምልኬ ፡ አልጠግብ ፡ አልኩ ፡ ጌታዬ
አንግሼ ፡ አልጠግብ ፡ አልኩ ፡ ወዳጄ
አጣሁ ፡ አጣሁኝ ፡ አንተን ፡ የሚተካ
በምድር ፡ በሰማይ ፡ አንደኛ ፡ ነህ ፡ ለካ (፪x)
ምነው ፡ ሌላ ፡ ቋንቋ
ሌላ ፡ ሌላ ፡ ቋንቋ
ቢኖረኝ/ቢፈጠር ፡ ልብን ፡ የሚያረካ (፪x)
አልወጣልህ ፡ አለኝ ፡ ከልቤ
እስቲ ፡ ላመስግንህ ፡ ጌታዬ ፡ ጌታዬ
አዝ፦ ያለኝ ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ ያለኝ (፬x)
አጣሁልህ ፡ እየሱስ ፡ አንተን ፡ መሳይ
የከበረ ፡ በምድር ፡ በሰማይ
ፍቅርህ ፡ ልቤን ፡ ጥብቅ ፡ አድርጐ ፡ ይዞታል
እስቲ ፡ ዘምር ፡ አመስግን ፡ ያሰኘናል
ሥምህ ፡ የከበረ ፡ የገነነ ፡ ነዉ ፡ ነዉ
ዝናህ ፡ የከበረ ፡ የገነነ ፡ ነዉ ፡ ነዉ
ጌታ ፡ ነህ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ
እንዳንተ ፡ ያለ ፡ በምድር ፡ የለም ፡ በሰማይ (፪x)
ሰው ፡ ያለኝ ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ እያለ ፡ ሲያወራ
የእኔ ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የለውም ፡ እኩያ (፪x)
አዝ፦ ያለኝ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ ያለኝ (፪x)
ያለኝ ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ ያለኝ (፪x)
አምልኬ ፡ አልጠግብ ፡ አልኩ ፡ ጌታዬ
አንግሼ ፡ አልጠግብህም ፡ አልኩ ፡ ወዳጄ
አጣሁ ፡ አጣሁኝ ፡ አንተን ፡ የሚተካ
በምድር ፡ በሰማይ ፡ አንደኛ ፡ ነህ ፡ ለካ (፪x)
ምነው ፡ ሌላ ፡ ቋንቋ
ሌላ ፡ ሌላ ፡ ቋንቋ
ቢኖረኝ/ቢፈጠር ፡ ልብን ፡ የሚያረካ (፪x)
አልወጣልህ ፡ አለኝ ፡ ከልቤ
ውለታህ ፡ በዛብኝ ፡ ጌታዬ ፡ ጌታዬ
አልወጣልህ ፡ አለኝ ፡ ከልቤ
እስቲ ፡ ላመስግንህ ፡ ጌታዬ ፡ ጌታዬ
አዝ፦ አዝ፦ ያለኝ ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ ያለኝ (፬x)
|