From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
በላይ ፡ በላዩ ፡ ላይ ፡ በረከት ፡ አዞልኛል
አንዱን ፡ ሳልጨርሰው ፡ ሌላው ፡ ይከተለኛል
ገና ፡ ሳልፈጽመው ፡ የጥያቄዬን ፡ ቃል
መልሴ ፡ በደጅ ፡ ቆሞ ፡ በር ፡ ያንኳኳልኛል
አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል (፪x)
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)
ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)
ጭንቅ ፡ አይለዉም ፡ ልቤን ፡ ፍርሃት ፡ ፍርሃት
ምን ፡ በወጣኝ ፡ ልፍራ ፡ ጌታ ፡ ሆኖኝ ፡ አባት
የሰማዩ ፡ ወፎች ፡ ጠግበው ፡ ከአደሩ
እንዴት ፡ እኔ ፡ አልኖርም ፡ እነሱ ፡ ከኖሩ
አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል
ኑሮዬን ፡ የምስጋና ፡ አድርጐታል
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)
ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)
ስለለመድኩኝ ፡ ነው ፡ የታምራት ፡ ኑሮ
ቀርቷል ፡ አትበሉኝ ፡ ተዓምርማ ፡ ድሮ
ተዓምር ፡ የፈለገ ፡ ወደዚህ ፡ ይመልከት
ዝንድሮም ፡ ይሰራል ፡ ጌታ ፡ በኛ ፡ ሕይወት
አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል (፪x)
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)
ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)
እንደዘመርኩት ፡ ነው ፡ ኑሮዬ
መሠረቴ ፡ ሆኗል ፡ ጌታዬ
ወጀቡ ፡ ቢበዛ ፡ ቢያይልም
ቢገፋኝ ፡ የሚገፋኝ ፡ አልወድቅም (፬x)
እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)
|