ኑሮዬን ፡ የታምራት (Nuroyien Yetamrat) - አውታሩ ፡ ከበደ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
አውታሩ ፡ ከበደ
(Awtaru Kebede)

Awtaru Kebede 4.jpg


(4)

ሌሊቱ ፡ ነጋ
(Lelitu Nega)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 6:46
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአውታሩ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Awtaru Kebede)

በላይ ፡ በላዩ ፡ ላይ ፡ በረከት ፡ አዞልኛል
አንዱን ፡ ሳልጨርሰው ፡ ሌላው ፡ ይከተለኛል
ገና ፡ ሳልፈጽመው ፡ የጥያቄዬን ፡ ቃል
መልሴ ፡ በደጅ ፡ ቆሞ ፡ በር ፡ ያንኳኳልኛል

አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል (፪x)
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)

ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ

እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)

ጭንቅ ፡ አይለዉም ፡ ልቤን ፡ ፍርሃት ፡ ፍርሃት
ምን ፡ በወጣኝ ፡ ልፍራ ፡ ጌታ ፡ ሆኖኝ ፡ አባት
የሰማዩ ፡ ወፎች ፡ ጠግበው ፡ ከአደሩ
እንዴት ፡ እኔ ፡ አልኖርም ፡ እነሱ ፡ ከኖሩ

አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል
ኑሮዬን ፡ የምስጋና ፡ አድርጐታል
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)

ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ

እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)

ስለለመድኩኝ ፡ ነው ፡ የታምራት ፡ ኑሮ
ቀርቷል ፡ አትበሉኝ ፡ ተዓምርማ ፡ ድሮ
ተዓምር ፡ የፈለገ ፡ ወደዚህ ፡ ይመልከት
ዝንድሮም ፡ ይሰራል ፡ ጌታ ፡ በኛ ፡ ሕይወት

አዝ፦ ኑሮዬን ፡ የታምራት ፡ አድርጐታል (፪x)
የኔ ፡ እኮ ፡ ከሰው ፡ ሁሉ ፡ ለየት ፡ ይላል (፪x)

ትላንትናን ፡ አኑሬሃለሁ ዛሬን ፡ ደግሞ ፡ በታምራቴ
ይልቅስ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ
ሂድ ፡ እንጂ ፡ ተረጋግተህ ፡ ኑር ፡ ይለኛል ፡ ረድዔቴ

እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)

እንደዘመርኩት ፡ ነው ፡ ኑሮዬ
መሠረቴ ፡ ሆኗል ፡ ጌታዬ
ወጀቡ ፡ ቢበዛ ፡ ቢያይልም
ቢገፋኝ ፡ የሚገፋኝ ፡ አልወድቅም (፬x)

እረጋጋለሁ ፡ አንተ ፡ ካልክማ
ልቤ ፡ ሰምቶሃል ፡ ቃልህን ፡ ጌታ (፪x)