From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
aster
አዝ፦ ቀድሞም ፡ ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈህ
ተገብቶህ ፡ እንጂ ፡ ማን ፡ ሰጥቶህ ፡ ያውቃል ፡ ስለጎደለህ
አንሶብህ ፡ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ አደባባይ ፡ ወጥተህ ፡ ማትለምን
ኢየሱሴ ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ ምትደነቅ (፪x)
ቀን ፡ አንድ ፡ ተብሎ ፡ ሳይጀመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ወር ፡ አንድ ፡ ተብሎ ፡ ሳይቆጠር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ዓመት ፡ በዓመት ፡ ላይ ፡ ሳይደመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
በዘመናት ፡ ዘመን ፡ ሳይጨመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ሳይባል ፡ በመጀመሪያ ፡ ሳትፈጥር ፡ ሰማይና ፡ ምድርን
አዕዋፋት ፡ ባየር ፡ ላይ ፡ ሳይበሩ ፡ ሳትመሰርት ፡ በፊት ፡ ተራሮችን
ገና ፡ ሳታበጅ ፡ ሰውን ፡ በጅህ ፡ ሳይወጣ ፡ እስትንፋስ ፡ ከአፍህ
ሁሉ ፡ ነገር ፡ ምንም ፡ ባዶ ፡ እያለ ፡ ምሥጋናህ ፡ ግን ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈ
አዝ፦ ቀድሞም ፡ ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈህ
ተገብቶህ ፡ እንጂ ፡ ማን ፡ ሰጥቶህ ፡ ያውቃል ፡ ስለጎደለህ
አንሶብህ ፡ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ አደባባይ ፡ ወጥተህ ፡ ማትለምን
ኢየሱሴ ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ ምትደነቅ (፪x)
ቀን ፡ አንድ ፡ ተብሎ ፡ ሳይጀመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ወር ፡ አንድ ፡ ተብሎ ፡ ሳይቆጠር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ዓመት ፡ በዓመት ፡ ላይ ፡ ሳይደመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
በዘመናት ፡ ዘመን ፡ ሳይጨመር ፡ አንተኮ ፡ ስትመለክ ፡ ነበር
ሳይባል ፡ በመጀመሪያ ፡ ሳትፈጥር ፡ ሰማይና ፡ ምድርን
አዕዋፋት ፡ ባየር ፡ ላይ ፡ ሳይበሩ ፡ ሳትመሰርት ፡ በፊት ፡ ተራሮችን
ገና ፡ ሳታበጅ ፡ ሰውን ፡ በጅህ ፡ ሳይወጣ ፡ እስትንፋስ ፡ ከአፍህ
ሁሉ ፡ ነገር ፡ ምንም ፡ ባዶ ፡ እያለ ፡ ምሥጋናህ ፡ ግን ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈ
ቀድሞም ፡ ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈህ
ተገብቶህ ፡ እንጂ ፡ ማን ፡ ሰጥቶህ ፡ ያውቃል ፡ ስለጎደለህ
አንሶብህ ፡ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ አደባባይ ፡ ወጥተህ ፡ ማትለምን
ኢየሱሴ ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ ምትደነቅ
|